[tubepress video=”WxUGItdRLFs”]
|
|||||||
[tubepress video=”WxUGItdRLFs”] [tubepress video=”gVTkMCr5txc”] [tubepress video=”R9nyozRfzzs”] [tubepress video=”6d7gj5M2-GE”] ለውጥ ከሩቅ አይመጣም ከቅርብ እንጂ፡፡ ለአንድ ግለሰብ መለወጥ ለውጥ ከውስጡ እንዲመጣ ያስፈልጋል፡፡ ለአንድ ቤተሰብ መለወጥ ደግሞ የቤተሰቡ አባላት መለወጥ የግድ ነው፡፡ ለአንድ ማዕበረሰብ ደግሞ እያንዳንዱ ቤተሰብ የሚያዋጡት ድምር ውጤት ከፍተኛ ሚና አለው፡፡ ስለዚህ ሀገር እንዲለወጥ እያንዳንዳችን መለወጥ ይኖርብናል፡፡ ይህንን ክታብ የከተብኩት ፕሬዝደንት ኦባማ ተመርጠው የለውጥ ዜና ትኩሳት ሳይበርድ ነው፡፡ ለውጥ!/Change!/ የሚለውን ሞቶ ይዘው የተነሱት ፕሬዝደንት ኦባማ ያሰቡትን ለማሳካት ከሁለት ዓመት በላይ የፈጀው የምረጡኝ ዘመቻው ብቻ ሳይሆን ለአሜሪካ ሕዝብ ገዝፎ የታየው ማንነታቸው ነው፡፡ ምንም እንኳን ዘረኝነት በአሜሪካ እጅግ የሳሳ ቢሆንም እነ ማርቲን ሉተር ኪንግ የጀመሩት ትግል ብዙ ትውልድ እንኳ ሳይተካ ጥቁር የአሜሪካ ፕሬዝደንት ይሆናል ብሎ ያሰበ የለም፡፡ ይህንን ታሪካዊ ክስተት ስናጣጥም እኔ መቼ ነው የምለወጠው? እኛ መቼ ነው የምንለወጠው? ኢትዮጵያ መቼ ነው የምትለወጠው? የሚል ጥያቄ አይምሮ ከመጠየቅ ወደ ኋላ አይልም፡፡ እንደኔ አመለካከት እያንዳንዳችን ከተለወጥን ፤ ሁለ ገብ የሆነ ለውጥ ላይ ከሠራን ጊዜ ሊወስድ ቢችልም ቀላል ነው ባይ ነኝ፡፡ ፕሬዝደንት ኦባማ ለውጥ ያሉለትን አላማ አንግበው ስኬትን ለማግኘት አስተዳደጋቸው ፤ በትምህርት ያላቸው ውጤት ፤ በበጉ አድራጎት ሥራ (Community Service) ያደረጉት አስተዋጽኦ ፤ በሥራው ዓለም የነበራቸው ስኬት ፤ በፓለቲካው ጅምራቸው የነበረው ውጤታማነት ሁሉ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡ በእኛ ማኅበረሰብ ውስጥ ለሀገር እድገት እና ለውጥ በፓለቲካው መድረክ ከመሳተፍ ያለፈ ድርሻ ያለ አይመስልም፡፡ ተምሮ በተማረበት ዘርፍ ስኬታማ መሆን፤ […] በዲያስፓራ ለምንኖር ኢትዮጵያን ከፊት የተቀመጠልን ትልቅ የቤት ሥራ ቢኖር ተተኪ ትውልድ ማፍራት ነው፡፡ በሀገር ቤት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የተሻለ ትውልድ መቅረጽ እንጂ ተተኪ ትውልድ ማፍራ አጀንዳቸው ላይሆን ይችላል፡፡ኢትዮጵያዊነት ፤ ማንነት ፤ ቋንቋ ፤ ባህል ፤ ሃይማኖትና ሥነ ምግባር በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ተምሮ ማደግ የሚቻልበት ሀገር በመሆኑ፡፡ ከጎረቤት፤ ዘመድ አዝማድ፤ ጋደኛ ወዘተ የምንማራቸው የማንነታችን መሠረት የሆኑ ብዙ ዕሴቶች መኖራቸውን ሀገሬን ለቅቄ በባዕድ ሀገር መኖር ስጀምር ነው የተረዳሁት፡፡
በስደት ላለን ኢትዮጵያዊያን ልጅ ማሳደግ ቀላል እንዳልሆነ መናገር ለቀባሪው አረዱት አይነት ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ልጆቼን እይልኝ ገበያ ደርሼ እመጣለሁ ከሚባልበት ሃገር መኪና ስር ቁጭ አድርጎ ዕቃ ማቀበል ወደማይቻልበት ሀገር መምጣት እንዴት አስቸጋሪ አይሁን፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያ እኛ ተጨንቀን ለልጆቻችን የማናደርግላቸው እነርሱ ግን አብረዋቸው ከሚያድጉ ሕጻናት ፤ ከቤተሰባቸው ፤ ከጎረቤት ወዘተ የሚማሩት ብዙ ቁም ነገር አለ፡፡ ምን አልባት ልጁ እንዴት ቋንቋ እንደተማረ የማያውቅ ብዙ አባት ይኖራል፡፡ በውጪው ሀገር ግን ይህ ዕድል በቀላሉ የለም ፤ እያንዳንዱን ነገር ከቤተሰብ አሊያም ከቴሌቪዥን መስኮት ነው የሚማሩት፡፡
እንግዲህ ጊዜ የሌለው 16 ሰዓት የሚሠራ ወላጅ ሲሆን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ከቴሌቪዥን ወይም ከሚያድጉባቸው ዴይ ኬሮች ይሆናል ማለት ነው፡፡ ወልደው ለባዳ ይላሉ ይሔ ነው፡፡ ከልጅነታቸው ጀምሮ በፈረንጆቹ ቋንቋ አድገው በባህላቸው ተውጠው የሚያድጉ ኢትዮጵያዊያን ልጆችን ቤት ይቁጠራቸው፡፡ እንግሊዘኛ ቋንቋ ብቻ መናገሩን እንደ ሥልጣኔ የሚመለከት ወላጅም ሞልቷል፡፡ ልጆች የእንግሊዘኛውን ቋንቋ መማሪያ ጥሩ መንገድ እንደሆኑ አድርጎ የሀገሩን […] |
News
Political Groups |