Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

ዶ/ር አብይ አህመድ ከኃይለማርያም ደሳለኝ በምን ይለያሉ?

Dr Abiy Ahmed and Hailemariam Desalegn- PHOTO-EthioDaily

Dr Abiy Ahmed and Hailemariam Desalegn- PHOTO-EthioDaily

ዋዜማ ራዲዮ- ገዥው ግንባር መዋቅራዊና ፖለቲካዊ ለውጦችን ባያካሂድም የኦሕዴዱ ሊቀመንበር ዶክተር አብይ አሕመድ ወደ ጠቅላይ ሚንስትርነቱ መምጣታቸው በብዙ ወገኖች ዘንድ በተለይም በኦሮሞ ብሄር ተወላጆች ዘንድ የደስታ እና ተስፋ ስሜት ፈጥሯል፡፡ በርግጥ በእሳቸው አመራር ስር ኢሕአዴግ የሚከተለውን አካሄድ ጊዜ ወስደው በጥንቃቄ ማየት የሚፈልጉም ብዙ ናቸው፡፡ የተለያዩ ወገኖች የሚደሰቱበትና ተስፋ የሚያሳድሩበት የየራሳቸው ግልጽ እና ስውር ምክንያት ሊኖራው ይችላል፡፡ ሁሉም አሁን እያሳዩት ያለው ስሜት ግን ለመንግስት መልካም ዜና ነው የሆነለት፡፡

ዶክተር አብይ በፌደራል ደረጃ በቁልፍ ፖለቲካዊ መስሪያ ቤቶች ገና ልምድ ያላገኙ እና ከሞላ ጎደል ለአራት ኪሎ ፖለቲካ ራቅ ያሉ ቢሆኑም በመጠኑ ሕዝባዊ ወገንተኝነት ያሳየው ኦሕዴድ ሊቀመንበር መሆናቸው፣ የሕወሃትን አንጋፋ መሪዎች የፖለቲካ አስተሳሰብ እንደማይጋሩ መታመኑ እና በዕድሜም ጎልማሳ መሆናቸው ብዙዎችን አስደስቶ ሊሆን ይችላል፡፡ ሆኖም በኢሕአዴግ ውስጥ በለውጥ ናፋቂ አመራሮች እና በነባሩ አመራር መካከል የተራዘመ ዴሞክራሲያዊ የሃሳብ ትግል ተደርጎ ለውጥ ናፋቂው ቡድን በማሸነፉ ለሥልጣን የበቁ ሰው አይደሉም፡፡ ይልቁንስ ሕዝባዊ አመጹንና የፖለቲካ ቀውሱን ለማስታገስ ሲባል በተለይ በወለፈንድ ርዕዮተ ዐለም ላይ የተቸከለው የሕወሃት ነባር አመራር በመልካም ፍቃዱ ለሥልጣን እንዳበቃቸው መረሳት የለበትም፡፡

ዶክተር አብይ ከተሰናባቹ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በላይ የገዘፉ ፈተናዎች ነው የሚጠብቋቸው

አንዱ ፈተናቸው “የሽግግር ጠቅላይ ሚንስትር መሆን ይችላሉ? ወይስ የቀውስ ጠቅላይ ሚንስትር?” በሚለው ጥያቄ ዙሪያ የሚሽከረከር ነው፡፡ በርግጥ ይህ ጥያቄ በሥልጣን በሚቆዩበት ጊዜ ልክ እና በኢሕአዴግ የለውጥ ፍላጎት ላይ ይመሰረታል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ግን ሀገሪቱ ከገባችበት ቀውስ እንዴት እንደምትወጣ ኢሕአዴግ ገና ፍኖተ ካርታ ማውጣት ስላልቻለ ወይም ስላልፈቀደ ለብዙ ጊዜ የቀውስ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው፣ በብዙ ችግሮች ተተብትበው የመቆየት ዕድላቸው ሰፊ ይመስላል፡፡

በፓርላመንታዊ ሥርዓት ውስጥ ያሉ ጠቅላይ ሚንስትር መሆናቸው እንደተጠበቀ ሆኖ የኢሕአዴግ አመራር ደሞ ቡድናዊ በመሆኑ በግላቸው የፈለጉትን አዲስ ካቢኔ ለማቋቋም በቂ ሥልጣን አይኖራቸውም፡፡ የሥራ ዘመናቸውን የሚጀምሩት በመንግስትና ፓርቲ መካከል ግልጽ መስመር የሚያበጅ እና በብሄር ተዋጽዖ እና ብቃት በሌላቸው በፓርቲ ካድሬዎች የተሞላውን የመንግስት ቢሮክራሲ ዘመናዊ እና በሳይንስ የሚመራ ለማድረግ ሥርዓት ባልተዘረጋበት ሁኔታ ነው፡፡ ሀገሪቱ ከፓርቲ ካድሬ ከተሞላ ካቢኔ ተላቅቃ ለውስብስብ ችግሮቿ የሚመጥን ብቃት እና ዕውቀት ያለው እና በጋራ ሃላፊነት መንፈስ የሚሰራ ሙያተኛ ካቢኔ (technocratic cabinet) ሳይኖራት አንድ ጠቅላይ ሚንስትር የፈለገውን ያህል ቢፍጨረጨር ለውጥ የማምጣት ዕድሉ አናሳ ነው፡፡

የገዥው ግንባር አሰራር አዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር የፖሊሲ ማሻሻያ እንዲያመነጩ እና በማያወላ አመራር እንዲያስፈጽሙ የሚያስችላቸው አለመሆኑም ሌላ ተያያዥ መሰናክል ነው የሚሆንባቸው፡፡ በመሠረቱ በኢሕአዴግ አሰራር አንድ ግለሰብ ይቅርና የገዥው ግንባር አባል ድርጅቶችና የመንግስት መዋቅር በሙሉ ለኢሕአዴግ ርዕዮተ ዐለም፣ ፖሊሲዎችና መርሆዎች ሙሉ ተገዥ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር እና የግንባሩ ሊቀመንበር የሚሆን ግለሰብ የኢሕአዴግን ቀኖና ሙሉ አስፈጻሚ ነው፡፡

በተለይ ዶክተር አብይ እንደ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሁሉ የግንባሩ አስኳል ከሆነው ሕወሃት ውጭ የተመረጡት ስለሆኑ ለሩብ ክፍለ ዘመን ጭቆና የመረረውን ሕዝብ ወደ ቃል ኪዳኗ ምድር የሚያደርሱ ሐዋሪያ አድርጎ ማየት በምንም መልኩ የሚያዋጣ አይደለም፡፡ ለሩብ ክፍለ ዘመን የቆየው አወቃቀርና ፖሊሲ ባልተቀየረበት ሁኔታ ብዙዎች የሰነቁት ተስፋ እውን የሚሆነው በተለይ የሕወሃት እና የቀሪዎቹ አባል ድርጅቶች ፍቃደኝነት ሲታከልበት ብቻ ነው፡፡ ኢሕአዴግ ለአዲሱ ተመራጭ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሠረታዊ ለውጥ ለማድረግ እንዳልተዘጋጀ ደሞ መግለጫዎቹ ሁሉ ግልጽ እያደረጉ ነው፡፡

በቅርቡ ከኢሕአዴግ አደረጃጀቶች “ጠቅላይ ሚንስትሩ ኢሕአዴግ ነው!” የሚል ቋንቋ መሰማቱ ዶክተር አብይ ስለሚጠብቃቸው ጥብቅ የቡድን አመራር ፍንጭ የሚሰጥ ነው፡፡ እሳቸው ሊቀመንበር ሆነው ከመመረጣቸው ጥቂት ቀደም ብሎ የግንባሩ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ “ኢሕአዴግ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመሩን እንደገና አጠናክሮ ይገፋበታል” ሲል መግለጹም የዚሁ ፈተና አካል ነው፡፡

በገዥው ግንባር በኩል ስናየው ደሞ አዲሱ ተመራጭ በኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች መካከል አፍጥጠውና አግጥጠው የመጡትን የሥልጣን እና ሃብት ክፍፍል ቅሬታዎች ማስታረቅ እና እየላላ የመጣውን የግንባሩን አንድነት የመጠበቅ ፈተና አለባቸው፡፡ ለዚህ ጉዳይ ኢሕአዴግ የመፍትሄ አቅጣጫ ሊያበጅለት ይቅርና ገና በቂ ውይይት እንኳ እንዳላደረገበት መናገር ይቻላል፡፡

በፌደራሉ እና ክልል መንግስታት መካከልም ቢሆን የተዛባ የሥልጣን እና ሃብት ክፍፍል ቅሬታ አለ፡፡ ይሄ ቅሬታ በአማራ እና ኦሮሞ ሕዝብ አመጽም እንደ አንኳር ችግር ተነስቷል፡፡ እናም ለቅሬታው ፖለቲካዊና ሕገ መንግስታዊ ምላሾች እንዲያገኝ ሕዝቡ ከአዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር ብቁ አመራር ይጠብቃል፡፡ አዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር ይሄን ማድረግ ስለመቻላቸው ወደፊት የሚታይ ሆኖ ብዙ መሰናክሎች እንደሚጠብቋቸው ግን ግልጽ ነው፡፡

በድርጅት ደረጃ የኢሕአዴግን የማዋሃድ የቤት ስራም ከዶክተር አብይ ፊት የተደቀነ መሆኑ ሌላው ድርጅታዊ ፈተና ነው፡፡ ኢሕአዴግን ወደ አንድ ኅብረ ብሄራዊ ፓርቲ የማሸጋገር አጀንዳ በመጭው ክረምት በግንባሩ ጠቅላላ ጉባዔ ውይይት እንደሚደረግበት ስለተነገረ ለዚያ ዝግጅት በማድረግረገድ፤ ውህደቱ ድጋፍ ካገኘ ደሞ ለውጡ የሚቀሰቅሳቸውን የርዕዮተ ዐለም፣ የአወቃቀር እና የጥቅም ግጭቶች የማስታረቅ ከባድ ፈተና ፊት ለፊታቸው ተደቅኗል፡፡

ባጠቃላይ ከድርጅታዊ ጀርባቸው እና ፖለቲካ ልምዳቸው አንጻር በአስቸጋሪ ቀውስ ውስጥ ያለች ሀገር የሚመሩ በመሆናቸው ዐይኖች ሁሉ እሳቸው ላይ እንደሚያርፉ ጥርጥር የለውም፡፡ ለዚህ ሁሉ ውስብስብ ችግር ምን ዐይነት አመራር እነደሚሰጡ በመጭዎቹ ወራት ፍንጭ መታየቱ አይቀርም፡፡ ችግሩ ቋፍ ላይ ያለው ሕዝብ ምን ያህል መታገስ ይችላል? የሚለው ነው፡፡ [በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ የድምፅ ዘገባ ከታች ይመልከቱ]

The post ዶ/ር አብይ አህመድ ከኃይለማርያም ደሳለኝ በምን ይለያሉ? appeared first on Wazemaradio.

[…]

Ethiopia: Hiber Special Program with Ato Ayele Angelo

Ethiopia: Hiber Special Program with Ato Ayele Angelo […]

Budding Music Video Market

Hope Entertainment, Lomi, Minewshewa and DireTube currently dominate the online streaming music video market in Ethiopia. They cater the works of local artists and some even help produce the videos. There is of course nobody that purchases the output once a video other than these online hosting companies with TV stations playing music for free. […] […]

Up-and-coming media personality

Hannah Gebresilassie is an emerging and one of the very few journalists from the Horn of Africa working in a mainstream media in the United States. She is known to showcase her cultures of home proudly to a large audience and advocates for a slew of issues, including on the role of immigrants in the […] […]

The rise of Abiy “Abiyot” Ahmed

The Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) has always been secretive about its party affairs. This is particularly true with regards to the internal party processes by which its chairman and deputy chairman are named. The vast majority of the public had no idea how these positions were filled in the party; whether it is […] […]

BBN Daily Ethiopian News March 30, 2018

BBN Daily Ethiopian News March 30, 2018 […]

Tirunesh Dibaba: I Love Running because ….

The three-time Olympic gold medallist and nine-time world champion is one of the greatest female endurance runners of all-time. Here the 32-year-old Ethiopian legend and reigning Chicago Marathon champion explains her passion for running. “I was motivated and inspired to run from a young age because of the success my older sisters and my cousin […] […]

BBN Daily Ethiopian News March 29, 2018

BBN Daily Ethiopian News March 29, 2018 […]

Ethiopia: Ethiopian 3 New Flight Destinations

ethiopian airlines

Ethiopian Airlines, the largest Aviation Group in Africa and SKYTRAX certified Four Star Global Airline, has launched three new flights to Kisangani and Mbuji Mayi in the Democratic Republic of the Congo (DRC) and Nosy-Be in Madagascar today, March 27, 2018.

[…]

Ethiopia’s Prime Minister-Elect Abiy Ahmed to be sworn in on April 2

ADDIS ABABA – Ethiopia’s prime minister-elect Abiye Ahmed will be sworn in on Monday, its parliament said, after the ruling coalition chose him to succeed Hailemariam Desalegn as its chairperson. The ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front coalition on Tuesday voted in the 42-year-old, a retired lieutenant general from Ethiopia’s largest ethnic group, the Oromo, […] […]

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.