Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

News

Earlier
ዋዜማ- በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ታሪክ ከአምስት አስርት ዓመታት በኋላ የውጭ ባለሀብቶች በሀገር ውስጥ የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ላይ እንዲሰማሩ የሚፈቅድ የህግ ማእቀፍ ተጠናቆ ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን ዋዜማ ከተለያዩ ምንጮች ስምታለች። ለኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ ተከልሎ የነበረውን የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ስራን ለውጭ ዜጎች የሚፈቅደው ህግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሚመራው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ፤ ለኢትዮጵያውያን ተከልሎ የቆየውን የወጪ እና ገቢ ንግድን እንዲሁም የጅምላ እና ችርቻሮ ንግድን ለውጭ ባለሀብቶች የሚፈቅድ መመሪያ ተዘጋጅቷል ። ይህ የመንግስት እርምጃ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለውጪ ውድ ድር ክፍት የማድረግ ዓላማ ያለው ሲሆን ይህም ሀገሪቱ አለማቀፍ አበዳሪዎች ድጋፍ እንዲደርጉላት የተወሰደ እርምጃ ሊሆን እንደሚችል በጉዳዩ ላይ ያወያየናቸው ባለሙያዎች ነግረውናል። ተያያዥ ዘገባ በዚህ ማስፈንጠሪያ ዘልቀው መመልከት ይችላሉ። በመመሪያው ላይም የውጭ ዜጎች በሀገር ውስጥ በጅምላ እና ችርቻሮ ንግድ ላይ የሚሰማሩባቸው ሁኔታም ተቀምጧል ። በዚህም መሰረት ከነዳጅ እና ማዳበርያ ውጭ የትኛውም የውጭ ዜጋ ፤ ባለሀብትም ሆነ ኩባንያ በጅምላ ንግድ ላይ መሰማራት እንደሚችል በመመሪያው ተቀምጧል ። የጅምላ ንግዱንም ከሀገር ውስጥ አምራች ገዝቶም ሆነ ከውጭ አስገብቶ ማከናወን እንደሚችልም ይጠቅሳል ። በሌሎች ህጎች ለጅምላ ንግድ አስፈላጊ የሆኑ ዝቅተኛ የካፒታል መጠን እና ተያያዥ ህጎች እንዳሉ ሆነው ፤ የውጭ ባለሀብቱ በጅምላ ንግድ ላይ መሰማራት ከፈለገ ዘመናዊ የሆነ የገበያ መሰረተ ልማት ለመገንባት ከመንግስት ጋር ውል መግባት አለበት ፤ ከዚህም ባለፈ የጅምላ ንግዱን የሚያቀላጥፍ የሎጂስቲክስ ዝግጅት ማድረግ እንዳለበትም ተደንግጓል ። የንግድ እና ቀጠናዊ [...]
Fri, Apr 12, 2024
Source: Wazema Radio
ከማዳበሪያ እና ነዳጅ ውጪ ሌሎች ምርቶችን ማስገባትንም መመሪያው ለውጭ ባለሀብቶች ይፈቅዳል ዋዜማ- መንግስት ለበርካታ አመታት የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ብቻ እንዲሳተፉበት ተከልሎ የቆየው ቡናን ፣ ጫትን ፣ የቁም እንስሳትን እና ቆዳና ሌጦን ለውጭ ገበያ የመላክ ስራ ለውጭ ባለሀብቶች የሚፈቅድ መመሪያ ማዘጋጀቱን ዋዜማ ተረድታች። በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ በሚመራው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ የተዘጋጀው እና ዋዜማ የተመለከተችው ሰነድ (መመሪያ) መንግስት በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ውሳኔን ለመወሰን ያበቃውን ምክንያት ያትታል። የመመሪያው መግቢያ እንደሚለው ከሆነ የግብርና ምርቶቹን ለውጭ የመላኩ እና የአስመጪነትን ዘርፍ ለሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ብቻ መከለሉ የተጠበቀውን ውጤት እንዳላስገኘ ይገልጻል። ብሎም ከለላውን ለህገ ወጥ ተግባር የሚጠቀሙ አካላትን እንደፈጠረ ፣ ላልተገባ ውድድር መንገድን እንደከፈተ ፣ በርካታ ቅሬታዎችን እንዳስከተለ እና ጥራት ያለው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማከናወንም እንዳላስቻለ አክሎም ገልጿል። መመሪያው አክሎም በእያንዳንዱ የወጪ ንግድ ዘርፎች ለመሰማራት የሚፈልጉ የውጭ ባለሀብቶች ማሟላት ያለባቸውን መስፈርቶች ዘርዝሯል። በመመሪያው መሰረት ከኢትዮጵያ ገበያ ጥሬ ቡናን ገዝቶ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የሚፈልግ የውጭ ባለሀብት ላለፉት ተከታታይ ሶስት አመታት፣ ቢያንስ በአማካይ በየአመቱ ከኢትዮጵያ 10 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ ቡናን የገዛ መሆን እንደሚጠበቅበት እና ፍቃዱን ባገኘበት አመት ቢያንስ 10 ሚሊየን ዶላር የሚያወጣ ቡናን መላክ እንደሚችል የንግድ ውልን ማቅረብ እንደሚጠበቅበትም መመሪያው ያዛል። ሆኖም የውጭ ባለሀብቱ ከኢትዮጵያ ቡና የመግዛት ታሪክ የሌለው ከሆነ ቡና የመላክ ፍቃድን ለማግኘት የተረጋገጠ እና አስተማማኝ ገበያ ያለው መሆኑን የሚያሳያ ሰነድ እና ፍቃድ ባገኘበት አመት 12.5 ሚሊየን [...]
Thu, Apr 11, 2024
Source: Wazema Radio
ዋዜማ- መንግስታዊው የፖሊሲ ባንክ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጊዜያዊት ብድር መልቀቅ ማቆሙን ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች ። ንግድ ባንኩ ብድር ለማግኘት የተለያዩ ሂደቶችን አልፈው ፤ ብድሩ ተፈቅዶላቸው የመልቀቅ ሂደት ላይ ያሉትም እንዲቆም ነው ያዘዘው ። ባንኩ ይህን ትእዛዝ ያስተላለፈው ረቡዕ መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ/ም መሆኑንም ሰምተናል ። ዋዜማ እንደሰማችው ከሆነ ፤ ንግድ ባንኩ በጊዜያዊነት ብድር መልቀቅ ከማቆሙ በስተቀር ባስተላለፈው ትእዛዝ ላይ ብድር መልቀቅ ያቆመበትን ምክንያት አልገለጸም። ሆኖም ከብድር መልቀቅ መለስ ያሉት የብደር ጥያቄ እና ሂደቶቹ አለመቆማቸውን ሰምተናል ። መንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ እስከ ዛሬ የሰጠው ብድርም ሆነ የሰበሰበው ቁጠባ ከአንድ ትሪሊየን ብር ያለፈ ብቸኛ ባንክ መሆኑ የሚታወቅ ነው ። ባንኩ በቅርቡ በተገበረው የሲስተም ማሻሻያ ሳቢያ በተፈጠረ ስህተት 801 ሚሊየን ብር ለምዝበራ ተዳርጎበት እንደነበረ እና ከዚህ ውስጥ አብዛኛውን ገንዘብ ባደረገው ክትትል ማስመለሱን የባንኩ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ በሰጡት መግለጫ ተናግረው ነበር ። ባንኩ ገንዘቡን የማስመለስ አካል ነው ያለውን ባልተገባ የገንዘብ ዝውውር ውስጥ ተሳትፈዋል ያላቸውን ደንበኞች ፎቶ ሳይቀር ለህዝብ ይፋ አድርጓል ። አሁን በጊዜያዊነት ብድር መልቀቅ ማቆሙ ከዚህ ጋር ይገናኝ አይገናኝ ለማድረግ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፈው አመት ብቻ 151 ቢሊየን ብር ብድር የሰጠ ሲሆን ፤ በተመሳሳይ አመት 165 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ቁጠባን ደግሞ ሰብስቦም ነበር ።ሆኖም ይህ በጀት አመት ከገባ ግን የቁጠባ አሰባሰቡ ከእቅዱ ጋር እየሄደ አለመሆኑ ተሰምቷል ። ለአብነትም [...]
Mon, Apr 08, 2024
Source: Wazema Radio
ዋዜማ– በትግራይ፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ከ4 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች በጦርነትና ድርቅ ሳቢያ  ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ዋዜማ ከየክልሎቹ ያሰባሰበችው መረጃ ያመለክታል። ትግራይ ከጦርነቱ በኋላበትግራይ ክልል ብቻ እስካሁን ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት አለመመለሳቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለዋዜማ ገልጧል።  ቢሮው ከጦርነቱ በፊት (2012 ዓ.ም) 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ተማሪዎች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ እንደነበር ጠቅሶ፣ በዘንድሮው ዓመት ከዚህ ቀደም ያቋረጡትን እና ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱትን ጨምሮ፣ 2 ነጥብ 4 ሚሊየን ተማሪዎች በትምህርት ላይ ይገኛሉ የሚል ዕቅድ እንደነበረው ገልጿል። ሆኖም የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ረዳኢ ገብረእግዚአብሔር ለዋዜማ እንደነገሯት፣ በ2016 የትምህርት ዘመን የተመዘገቡት ጠቅላላ ተማሪዎች ቁጥር ከ1 ሚሊዮን በታች ነው። ከተመዘገቡት መካከልም ድርቅ ባስከተለው ርሃብ ምክንያት ትምህርታቸውን የሚያቋርጡ ተማሪዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው፣ ባለፈው የካቲት ወር ብቻ ከ20 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ማቋረጣቸውን ገልጸዋል።  በ57 ወረዳዎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች በተደረገ ዳሰሳም፣ በ625 ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ከ223 ሺሕ በላይ ለሚሆኑት ተማሪዎች አስቸኳይ የምግብ አቅርቦት (ምገባ) ካልተከናወነ በስተቀር ትምህርታቸውን ማቋረጣቸው አይቀሬ ነው ብለዋል።  ከመጭው መስከረም ወር በፊት እህል ስለማይደርስ እየተባባሰ በሚሄደው ርሃብ እና ድርቅ የተነሳ ትምህርታቸውን የማይጨርሱ ታዳጊዎች ቁጥር አሁን ካለበትም በላይ ይጨምራል ሲሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል።  በተስፋ መቁረጥ፣ ርሃብ እና መፈናቀል ምክንያት ወደ ትምህርት ቤት መመለስ ያልፈለጉ ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች፣ በስደት፣ በልመና እና ሌሎች ችግሮች ውስጥ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። የክልሉን ተማሪዎች በ2018 [...]
Wed, Apr 03, 2024
Source: Wazema Radio
ዋዜማ- የሱማሊያዋ ፑንትላንድ ራስ ገዝ፣ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሃመድ ለሚመሩት የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት እውቅና መንፈጓንና ከፌደሬሽኑ በይፋ ለቅቃ መውጣቷን ቅዳሜ’ለት አስታውቃለች። ፑንትላንድ፣ ኹሉም የሚስማማበት የፌደራል ሕገመንግሥት በሕዝበ ውሳኔ እስኪጸድቅ ድረስ፣ ራሴን የቻልኩ ሉዓላዊ አገር ኾኛለሁ በማለት ነው ያወጀችው። ፑንትላንድ ከዓለማቀፍ ድርጅቶችም ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደምትጀምር ገልጣለች። ፑንትላንድ ራስ ገዝ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰችው፣ የሱማሊያ ፓርላማ አወዛጋቢ ከኾነው የሕገመንግሥት ማሻሻያ ከፊሎቹን ማሻሻያዎች ማጽደቁን ተከትሎ ነው። የሕገ መንግሥት ማሻሻያው፣ አገሪቱ በፓርላሜንታዊ የመንግሥት አወቃቀር ፋንታ ፕሬዝዳንታዊ የመንግሥት አወቃቀር እንድትከተል፣ የጠቅላይ ሚንስትርነት ሥልጣን እንዲቀር እና የጎሳ ውክልናን መሠረት ባደረገው የምርጫ ሥርዓት ፋንታ የአንድ ሰው አንድ ድምጽ ቀጥተኛ የምርጫ ሥርዓት እንዲኖር የሚደነግግና ሌሎች ማሻሻያዎችን ያካተተ ነው። ፑንትላንድ ከፌደሬሽኑ መውጣቷን ብታውጅም፣ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሃመድ ግን ፓርላማው ያጸደቃቸውን ከፊል ማሻሻያዎች ትናንት በፊርማቸው አጽድቀው የአገሪቱ ሕግ አድርገዋቸዋል። ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሃመድ ሥልጣን ከያዙ ጀምሮ፣ ላለፉት 12 ዓመታት ሲንከባለል የቆየው የአገሪቱ ጊዜያዊ ሕገመንግሥት አንዳንድ ማሻሻያዎች እንዲደረጉበት የፌደሬሽኑን አባል መንግሥታት ሲያግባቡ ቆይተው ነበር። በዚህ ጥረታቸው ከፑንትላንድ በስተቀር የሁሉንም ፌደራል ግዛቶች ይሁንታ ማግኘት ችለዋል። በተቃውሞው ጎራ በኩል ደሞ፣ ፑንትላንድ ብቻ ሳትሆን የቀድሞ የአገሪቱ ፕሬዝዳንቶችም ሕገመንግሥታዊ ማሻሻያውን በጥብቅ ይቃወሙታል። የሕገመንግስታዊ ማሻሻያው የተቃውሞ መነሻ፣ ማሻሻያው ጊዜያዊውን ሕገመንግሥት ከሥረ መሠረቱ የሚቀይር፣ ሥልጣን በፕሬዝዳንቱ እጅ እንዲከማች የሚያደርግና ለአምባገነንነት በር የሚከፍት እና በቂ ውይይትና መግባባት ያልተደረሰበት ነው የሚል ነው። ተቃዋሚዎቹ፣ ሕገመንግሥታዊ ማሻሻያው የፕሬዝዳንቱ የግል ፍላጎት እንጂ የሕዝቡ ፍላጎት ነጸብራቅ አይደለም የሚል [...]
Mon, Apr 01, 2024
Source: Wazema Radio
“ባለፉት 50 ዓመታት የተከሰቱት ጦርነቶች የተጀመሩት ሚዲያው ባስተጋባው ውሸት መሆኑን ደርሼበታለሁ” ጁሊያን አሳንዥ፤ የዊኪሊክስ መሥራች። የአገራችን ሚዲያ አውታሮች በተለይም የግሉ ሚዲያ የሚባሉትና በ1997 ምርጫ ወቅት የነበሩት በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እንዲቀጭጭ፣ የሃሳብ ልዩነት እንዳያድግ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና አመራሮች ጉያ ሥር ገብተው የፈጸሙት ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው። ለቀጣዩ ትውልድ መማሪያ ይሆን ዘንድ በወጉ ተጠንቶና ተሰንዶ ሊቀመጥ ይገባል። ምክንያቱም ከዚያን ጊዜ […] [...]
Thu, Feb 15, 2024
Source: Goolgule
* በ“ጋዜጠኛነት” ስም የሚፈጸመው የሚዲያ ሸፍጥ በትግራይ ክልል “ከ200 በላይ ኢንዱስትሪዎች ሥራ ጀምረዋል” በሚል ፓርላማ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበው ሪፖርት “ከእውነት የራቀ ነው” ሲሉ የከሰሱት የትግራይ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ 212 ኢንዱስትሪዎች ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ሥራ እንዲጀመሩ ክስ ባቀረቡበት ዜና ጎን ለጎን አስታወቁ። ዜናው የክስ ሳይሆን አሃዱና ቲክቫህ በቅብብሎሽ አንዱ ሌላውን ዋቢ አድርገው ባሰራጩት ዜና […] [...]
Tue, Feb 13, 2024
Source: Goolgule
በአዲስ አበባ እምብርት ፒያሳ፤ የሚኒሊክ ሀውልት እና የአራዳው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚያዋስኑት ግዙፍ ፕሮጀክት ነው። በቅርቡ ከታደሰው እና የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ከሚገኝበት ማዘጋጃ ቤት ጋር ደግሞ በድልድይ ተገናኝቷል። እስከ ዛሬ ድረስ የራሱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ሳይኖረው የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤትም ቋሚ መሰብሰቢያ አዳራሽ የሚያገኘው በዚህ ፕሮጀክት ነው። እየተጠናቀቀ ያለው ይህ […] [...]
Tue, Feb 13, 2024
Source: Goolgule
ኢትዮጵያ ነጻነቷን ጠብቃ እንድትኖር ያደረጓት አባቶቻችንን የሚዘክር የዓድዋ ድል መታሰቢያ በአዲስ አበባ ፒያሳ ተገንብቶ ዛሬ ይመረቃል። መታሰቢያው የተገነባው ጀግኖች ወደ ጦርነቱ ሲተሙ በአንድነት ተሰባስበው ጉዟቸውን የጀመሩበት ቦታ ላይ ነው። የዓድዋ ድል መታሰቢያ ላይ የሚታየው 00 ኪሎ ሜትር መነሻ ቦታ የኮምፓስ ምልክት በአዲስ አበባ እንዲሁም በመላ ኢትዮጵያ ለሚገኙ ቦታዎች የርቀት መለኪያ መነሻ ነው። የዓድዋ ድል መታሰቢያ […] [...]
Sun, Feb 11, 2024
Source: Goolgule
ትግራይን ማቃናት ያቃተው ካድሬ – አቅቶሃል ተባለ “ሰላሳ ሰባት ሚሊዮን ብር ለትግራይ አስተዳደር መሰጠቱን ስንሰማ ደንገጠናል። ዜናውን የሰሙ ሁሉ ብሩ የት ገባ? የሚል ጉምጉምታ እያሰሙ ነው። አካል ጉዳተኞች ጸጉራቸውን እየነጩ ነው። ጉዳዩን ትግራይ ያሉ ፖለቲከኞችም እየመከሩበት ነው። ሕዝብ ተናድዷል” ስትል ተቀማጭነቷ አዲስ አበባ የሆነ የትግራይ ተወላጅ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ተባባሪ ነግራዋለች። ወጣቷ በጦርነቱ አንድ ወንድሟን […] [...]
Sat, Feb 10, 2024
Source: Goolgule
This site has moved. Please click on the following link. Ethiopia Observer [...]
Sat, Apr 26, 2014
Source: Arefe
a-bakery-in-addis
Private media are reporting a bread shortage in Addis Ababa, where residents of the city are complaining about their difficulty to find affordable, smaller size breads. Addis Guday a weekly Amharic magazine, says the lack of flour might have led to bread shortages in the city, quoting some bakery owners. The magazine also said there has been slight price increase in some food items that are made with wheat flour. A quick survey conducted by the magazine staff in some bakeries of the city conformed that there has indeed been an acute bread shortage in the city, especially the often consumed smaller size breads. The breads that were mostly available were those bigger ones, which cost around ten birr. The Ethiopian government has not acknowledged a bread and wheat shortage in the city. Addis Guday quoted Kelemework, vice-chair of the Ethiopian Agricultural Agency, as saying he is not aware of the city’s bread crisis. Bread is a staple in the Ethiopian diet, eaten with almost every meal. People are largely dependent on private bakeries amid an acute bread shortage there. The government often says the country has enough wheat reserves for one year and a half. [...]
Sun, Apr 06, 2014
Source: Arefe
Alemayehu Geda
An Ethiopian researcher says it is the West, and not China, that still has the bigger economic impact on Africa. The professor of economics at Addis Ababa University, Alemayehu Geda told China Daily that while the current spotlight might be on the impact of the world’s second-largest economy on the continent, it is former colonial powers and the United States that are the largest investors. “The conclusion one would make from all the media coverage and even the views of ordinary people is that China is this huge foreign investor “Yet 90 percent of the (cumulative) foreign direct investment into Africa is still from the West, the United Kingdom, France and the US. China’s contribution is actually quite small. China combined with India is less than 6 percent. This gets lost in all the reports,” he says. Alemayehu, who is regarded as a leading authority on the Ethiopian economy and a renowned development economist says China has had its biggest impact on just a narrow select number of resource-exporting countries. The full story could be found at China Daily Africa website. [...]
Sat, Apr 05, 2014
Source: Arefe
Dr. segenet kelemu
Ethiopian scientist Doctor Segenet Kelemu has been named the 2014 African Laureate in the 16th annual L’Oréal-UNESCO For Women in Science Awards. Currently serving as a director general of the Nairobi-based International Center for Insect Physiology and Ecology, Dr. Segenet is the first Ethiopian to win the prestigious award. She joins five exceptional women scientists from around the world, one from each continent, who were recognized for their contribution to science at an awards ceremony, held at the Sorbonne in Paris last week (March 19) before an audience of personalities from the worlds of science, economics, academia and culture. The $100,000 award celebrates the outstanding achievements of women in science and is recognized as one of the premier international science awards. Dr. Segenet was honored for her research on how microorganisms living in symbiosis with forage grasses can improve their capacity to resist disease and adapt to environmental and climate change. Her work is providing new solutions for ecologically responsible food crop production especially by local, small-scale farmers. Born in Fenote Selam, Gojam, Segent did her high school studies in Debre Markos and begun her college education in Alemaya university and later did her master studies in Addis Ababa University. She [...]
Wed, Mar 26, 2014
Source: Arefe
Art Fair 011
For the first time in Addis Ababa, a massive art fair is offering contemporary Ethiopian art for sale to collectors and first-time buyers. Some 1 000m² of floor space at Boles Millennium hall is filled with a great visual feast with the inauguration of the four day Addis Art Fair, running from 15 to 18 March. The art showcase included its range of traditional works, like paintings, drawings and sculptures, as well as patchwork, installations, print and ceramics pieces from both established and promising newcomer artists. Addis Art Fair 2014 is organized by Elizabeth W.Giorgis, Bekele Mekonnen and Balcha Entertainment, with Derba Cement as the official sponsor. The organizers say the Addis Art Fair 2014 aims to make modern art attainable everyone and to encourage the average person to explore the breadth and depth of this thriving discipline. “It is a platform for young artists to exhibit their works and it also creates an opportunity for those who don’t have access to such venues,” the statement in the catalog reads. According to the organizers, art fairs are about the business of art, appealing to an audience that might ordinarily shy away from the gallery space. “They make art accessible by [...]
Tue, Mar 18, 2014
Source: Arefe

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.