Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

Ethiopia Commodity Exchange (ECX) Daily Trade Data – 26 March 2024

ECX Logo

Here is the daily commodity trade data from Ethiopia Commodity Exchange (ECX) for items traded on 26 March 2024.

[…]

ዘንድሮ ከ261 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ ፈላጊዎች ወደ ውጭ አገራት ተልከዋል

  • መንግስት ግማሽ ሚሊየን ዜጎችን በዚህ ዓመት ወደ ውጪ ሀገር ለመላክ እየሰራሁ ነው ብሏል

ዋዜማ- የሥራና ክህሎት ሚንስቴር በዘንድሮው ዓመት እስካሁን ባሉት ጊዜያት ከ261 ሺሕ በላይ ሥራ ፈላጊዎች መንግሥት የሥራ ስምሪት ውል ወደተዋዋለባቸው አገራት መላካቸውን ለዋዜማ ገልጿል።

በ2015 ዓ.ም ከ102 ሺሕ በላይ ሥራ ፈላጊዎች ወደ ውጭ አገራት መላካቸውን የገለጸው ሚንስቴሩ፣ በዘንድሮው ዓመት በውጭ አገራት እያደገ ከመጣው የሥራ ፍላጎት አንጻር 500 ሺሕ ዜጎችን ለመላክ ዕቅድ መያዙን የሚንስቴሩ የሕዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ አበበ አለሙ ለዋዜማ ተናግረዋል።

ወደ ውጭ ከተላኩት ውስጥ አብዛኞቹ ሴቶች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ የሥራ ስምሪቱም ከቤት ውስጥ ሥራዎች ጋር የተገናኘ ነው ተበሏል።

በአሁኑ ወቅት በመላ አገሪቱ ለውጭ አገራት የሥራ ስምሪት ብቻ የተመለመሉ 99 የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት መኖራቸው ገልጸዋል።

በዚህ ወቅት ወደ ውጭ የሚላኩ ሥራ ፈላጊዎች ለቤት ውስጥ ሥራ በመሆኑም፣ ተቋማቱ ከሶስት ወር የማይበልጥ ስለቤት ውስጥ ሥራዎች ስልጠና እና የብቃት መመዘኛ እየሰጡ እንደሚገኝ አበበ አስረድተዋል።

የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ሳውዲ አረቢያ ፣ ኳታር እና ጆርዳን ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነት ተፈራርመው ኢትዮጵያውያን ሥራ ፈላጊዎችን የሚቀበሉ መዳረሻ አገራት መሆናቸውን ነው የተናገሩት።

አሁን ላይ ከፍተኛ የሥራ ፍላጎት እየመጣ ያለው ከተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች መሆኑንም የገለጹት አበበ፣ ለሥራ የሚላኩ ዜጎች ከፓስፖርት እና ከምርመራ ወጪ በስተቀር ምንም ዓይነት ክፍያ እንደማይከፍሉ ተናግረዋል።

ሥራ አስፈጻሚው በቀጣይ መዳረሻ አገራቱን ለማብዛት ንግግርና ውይይት እያደረግንባቸው ያሉ አገራት አሉ ሲሉ ገልጸው፣ አገራቱን ንግግሩ ሲያልቅ ወደፊት እናሳውቃለን ብለዋል።

ሆኖም ወደፊት ሥራ ፈላጊዎችን ወደ አፍሪካ፣ አውሮፓና አሜሪካም ለመላክ በሰፊው መታሰቡን ነግረውናል።

መንግሥት የሰለጠኑ እና በከፊል የሰለጠኑ ዜጎችን ወደ ውጭ አገራት ለሥራ ለመላክ የረዥም ጊዜ ዕቅድ እንዳለው የጠቀሱት አበበ፣ ለሙከራ ወደ ጀርመን አገር የተላኩ መሃንዲሶች እንዲሁም “ወደ ሌላ አገር” የተላኩ ነርሶች መኖራቸውን ገልጸዋል።

የእነዚህ ባለሙያዎች ውጤት ታይቶ ሥራ ፈላጊ ዜጎችን አሰልጥኖ ወደ ተለያዪ አገራት ለመላክ በሰፊው መታቀዱን ነው የተናገሩት።

መንግሥት ለአገር ውስጥ ሥራ ፈጠራ ቅድሚያ ይሰጣል ያሉት ሥራ አስፈጻሚው፣ ነገር ግን ፍልሰትን ማስቀረት ስለማይቻል ዜጎች በህጋዊ መንገድ ደህነታቸው ተጠብቆ በውጭ አገራ ሥራ እንዲፈጠርላቸው እየሰራ ነው ብለዋል።

መንግሥት ዜጎችን ለሥራ ወደ ውጭ የሚልከው የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ነው የሚሉና ሌሎች አንዳንድ ተገቢ ያልሆኑ ክሶች እንደሚሰሙም ጠቁመዋል።

መንግሥት ዜጎችን ወደ ውጭ ሲልክ አንድም የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እንደማያስብ በማንሳት፣ በእርግጥም ከፍተኛ ገቢ እንደሚያስገኝ እና እንደ ቻይና ህንድና ፊሊፒንስ ባሉ አገራት የተለመደ አሰራር ነው ሲሉም ገልጸዋል።

መንግሥት ወደ ውጭ አገራት የሚላኩ ሥራ ፈላጊዎች የመብት ጥሰት እንዳይደርስባቸው እና ጥቅማጥቅማቸው እንዲከበር በየአገራቱ ካሉ የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች ጋር እንደሚሰራ እንዲሁም፣ ገንዘባቸውን በአገር ውስጥ እንዲያጠራቅሙ ከባንኮችና ከኢትዮ ቴኮም ጋር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

አበበ፣ የውጭ አገራት የሥራ ስምሪት ላይ ድርሻ ካላቸው ተቋማት ጋር በየወሩ ግምገማ መኖሩንም ነግረውናል።

ዋዜማ በአንዳንድ አካባቢዎች ወደ አውሮጳ አገራትና ወደ ካናዳ ትሄዳላችሁ ተብለው በመንግሥት ተቋማት የተመዘገቡና አሻራ የሰጡ፣ ወጣቶች መኖራቸውን ሰምታለች።

አበበ ግን በመንግሥት እገዛ ከአራቱ አገራት (የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ሳውዲ አረቢያ ፣ ኳታር እና ጆርዳን) ውጭ የሚላክ ሥራ ፈላጊ አለመኖሩን ጠቅሰው፣ በመንግሥት በኩል የሚመዘገቡ ሰዎች ስለሚሄዱበት አገር ቀድሞ እንደማይነገራቸው ገልጸዋል። [ዋዜማ]

The post ዘንድሮ ከ261 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ ፈላጊዎች ወደ ውጭ አገራት ተልከዋል first appeared on Wazemaradio.

The post ዘንድሮ ከ261 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ ፈላጊዎች ወደ ውጭ አገራት ተልከዋል appeared first on Wazemaradio.

[…]

Ethiopia Unearths Major Gold Deposits

Gold Benishangul Gumuz

The Ethiopian Ministry of Mines has announced the discovery of gold deposits exceeding 517 tons across several regions, including Benishangul-Gumuz, Gambella, Oromia, and Tigray. This discovery is the culmination of extensive geological surveys conducted over the past 15 years, according to Mines State Minister Million Mathewos.

[…]

Ethiopia's WTO Bid Shows Promise, Ministry of Trade and Regional Integration

MoTRI Logo

Ethiopia’s effort to joining the World Trade Organization (WTO) is inching closer to reality, according to the Ministry of Trade and Regional Integration (MoTRI). State Minister Kassahun Gofe, during a briefing to the House of People’s Representatives (HPR), highlighted the potential benefits of WTO membership, including expanded global trade opportunities for Ethiopia.

[…]

Ethiopian Electric Utility Expands Reach

EEU logo

The Ethiopian Electric Utility (EEU) is making significant strides in expanding electricity access and modernizing its services. As of the 2023/2024 fiscal year, the number of EEU customers has reached 4,615,787, reflecting a net gain of 257,188 new customers connected in just eight months.

[…]

Ethiopia: Mekele Industrial Park Reopens

Mekelle Industrial Park

The Mekele Industrial Park in Ethiopia is back in business. After a two-year pause due to the Tigray conflict, the Industrial Parks Development Corporation (IPDC) announced the park’s successful return to full-scale production. Existing companies have already restarted operations, and the park is attracting fresh interest from new investors.

[…]

Ethiopia Commodity Exchange (ECX) Daily Trade Data – 22 March 2024

ECX Logo

Here is the daily commodity trade data from Ethiopia Commodity Exchange (ECX) for items traded on 22 March 2024.

[…]

“የኦሮሞን ህዝብ ከቀየው አዲስ አበባ መግፋትና ማሳደድ አክትሞለታል” ሽመልስ አብዲሳ

ዋዜማ- የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በግፍና በኢ-ፍትሀዊነት ከቀየው ፊንፊኔ (አዲስ አበባ) እንዲሰደድ የተደረገውን የኦሮሞ ሕዝብ ወደ ቀደመ ስፍራው እንዲመለስ እያደረግን ነው ሲሉ በይፋዊ ማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ተናግረዋል።

የኦሮሞ ሕዝብ ለዘመናት ሲደርስበት በነበረው መገፋት የተነሳ ከተማዋን ለሌሎች ለቆ እስከመውጣት ደርሷል ያሉት ሽመልስ፣ይህም መገፋት ሄዶ ሄዶ እትብቱ በተቀበረባት ፊንፊኔ (አዲስ አበባ) የባዕድነት ስሜት እንዲሰማውና በራሱ ቀየ ላይ ባይተዋር እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል።

ከተማዋ በሌሎች የበላይነት ስር ሆና በተለይም የኦሮሞን ሕዝብ ለዘመናት እንደ ባዕድ የመመልከት አካሄድን ስትከተል ቆይታለች ያሉት ርዕሰ መሥተዳድሩ፣ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በከተማዋ አንዳችም የኦሮሞን ህዝብ ማንነት የሚገልጽ ምልክት (symbolic represention) አለመኖሩ ነበር በማለት ጠቁመዋል።

“ከዚህ በኋላ ግን መንግሥታችን፣ያለፈውን የውድቀት ታሪክ፣ጉዳትና መፈናቀል ማውራት፣ እንዲህ ተደረግን ብሎ ስሞታ ማቅረብ አይሻም” ሲሉ ገልጸዋል።

ይልቁንም የተገኘውን ዕድል በመጠቀም፣ትላንት በሕዝባችን ላይ ሲደርስ የነበረውን ግፍና በደል ለመካስ ብሎም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስቆም አዲስ ምዕራፍ ከፍተን ወደ ሥራ ገብተናል ብለዋል።

በዚህም መሠረት፣መንግሥት በግፍ ከቀየው የተፈናቀለውን ሕዝብ በመመለስ በከተማዋ በሁሉም ዘርፍ ካሉ ዕድሎች ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራ ይገኛልም ሲሉ ጠቁመዋል።

አዲስ አበባን በዚህ ወቅት ስንመለከት፣ በፖለቲካው፣በኢኮኖሚ፣በማኅበራዊ እንዲሁም በባሕል የሕዝባችንን ሰፊ ተሳትፎ የሚሹ እጅግ ግዙፍ የሆኑ ፕሮጀክቶች እየተሰሩ ይገኛሉ ያሉት ሽመልስ፣ይህም ሀሳባችንን ከግብ ለማድረስ ትልቅ መሳሪያ ይሆነናል ብለዋል።

እየተሠሩ ካሉት ከነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል፣የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣የኦቢኤን ሚዲያ ኮምፕሌክስ፣የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተፕራይዝ፣የኦሮሞ አርት ማሠልጠኛ ማዕከል፣የኦሮሞ ባሕላዊ ምግብ አሰራርና ዝግጅት ማዕከል፣የኦሮሞ ባሕላዊ እቃዎች ማሳያና የገበያ ማዕከል፣ሲንቄ ባንክ፣ቡሳ ጎኖፋ እንዲሁም የተለያዩ ኢንተርፕራይዞችን በጥቂቱ ማንሳት ይቻላል ሲሉ ገልጸዋል።

እስካሁን ያለው አፈጻጸም፣መንግሥት የሕዝባችንን የዘመናት ጥያቄና እውነትን ወደ ቦታዋ ለመመለስ እንዲሁም ቃል የተገባውን ለመፈጸም ያለውን ቁርጠኛነት ያሳየ ነው ብለዋል።

አሁንም የሕዝባችንን ያልተመለሱ ጥያቄዎች በሂደት ለመመለስ በትኩረት እንሰራለን ያሉት ርዕሰ መሥተዳድሩ፣ሕዝባችንን ከከተማው መግፋትና ማሳደድ ግን ከዚህ በኋላ አክትሞለታል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። [ዋዜማ]

The post “የኦሮሞን ህዝብ ከቀየው አዲስ አበባ መግፋትና ማሳደድ አክትሞለታል” ሽመልስ አብዲሳ first appeared on Wazemaradio.

The post “የኦሮሞን ህዝብ ከቀየው አዲስ አበባ መግፋትና ማሳደድ አክትሞለታል” ሽመልስ አብዲሳ appeared first on Wazemaradio.

[…]

መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ የግል ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ሙሉ በሙሉ አገደ

ዋዜማ- ከወራት ማመንታት በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ የግል አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ እገዳ መጣሉን መኪና አስመጪ ድርጅቶችና ተሽከርካሪ ለማስገባት የሞከሩ ግለሰቦች ለዋዜማ ተናግረዋል።

ምንጮቻችን እንደነገሩን ከመካከለኛው ምስራቅ፣ ከአውሮፓና ደቡብ አፍሪቃ ያጓጓዟቸውን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ማስገባት እንደማይችሉ ከሶስት ሳምንት በፊት ተነግሯቸዋል። በእገዳው ሳቢያ ከፍተኛ መጉላላትና ኪሳራ እንደደረሰባቸው ባለጉዳዮቹ ነግረውናል።

ከሳምንታት በፊት የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ማገዱን ለፓርላማ አባላት ሲያስታውቅ የገንዘብ ሚኒስቴር በበኩሉ እገዳው ተገባራዊ እንደማይደረግና በዕቅድ ደረጃ ያለ መሆኑን ተናግሮ ነበር።

ይሁንና ባለፉት ቀናት የተለየ ፍላጎት ላላቸው የልማት ፕሮጀክቶችና ለህዝብ ትራንስፖርት የሚውሉ ካልሆኑ በቀር በነዳጅ የሚሰሩ የግል ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር አይገቡም።

“እንዲህ አይነቱ አሰራር ተግባራዊ ከመደረጉ አስቀድሞ ዝግጅት እንድናደርግና ከውጪ ተጭነው በመንገድ ላይ ያሉና የውጪ ምንዛሪ የወጣባቸውን ተሽከርካሪዎች እንድናስረክብ ዕድል መሰጠት ነበረበት” ይላሉ በከተማዋ በአስመጪነት ስራ የተሰማሩ ባለሀብት።በመጪው ሳምንት ከትራስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር ጋር ለመነጋገር ማቀዳቸውንም ነግረውናል።

በውጪ ሀገር ከሀያ ዓመታት በላይ የቆየ ሌላ ግለሰብ ደግሞ አቅሜ የሚፈቅደውን አይነት ለግል መገልገያ ተሽከርካሪ ገዝቼ አስፈላጊውን የጎምሩክ መስፈርት ባሟላም፣ መኪናውን ማስገባት እንደማልችልና ወደመጣበት እንደመልሰው ተነግሮኛል ይላል።

መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ የግል ተሽከርካሪዎችን ያገደው የአካባቢ ብክለትን ለመከላከልና የነዳጅ ወጪውን ለመቀነስ መሆኑን ገልጿል።

ከሰሞኑ ለዋልታ መግለጫ የሰጡት የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚንስትሩ አለሙ ስሜ የነዳጅ መኪና ክልከላው ተግባራዊ መደረግ መጀመሩንና መንግስት የኤሌክትሪክ መኪና ላይ ከፍተኛ የቀረጥ ማበረታቻ ማድረጉን አረጋግጠዋል።

መንግስት በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የባትሪ መኪናዎችን እንደሚያበረታታና እንደሚያስፋፋም ሚንስትሩ አብራርተዋል።

ሚንስትሩ አክለውም ህብረተሰቡ በነዳጅ የማይሰሩ የትራንስፖርት አማራጮችንና የጋማ ከብትና ብስክሌት እንዲጠቁም ብሎም በግሩ መጓጓዝን ልማድ እንዲያደርግ መክረዋል።

ሚኒስቴሩ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች የሚውሉና የተለየ ምክንያት ላላቸው የግል ላልሆኑ ተቋማት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን እንዳማይከለክል አለሙ ስሜ ጠቁመዋል።

ይህ አሰራር የሀገሪቱ የአረንጓዴ ልማት አንድ አካል መሆኑንና “በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳብ አመንጪነት” በካቢኔ ውይይት ተደርጎበት ተግባራዊ መደረግ እንደጀመረም ሚንስትሩ አመልክተዋል።

በሀገር ውስጥ የሚገጣጠሙ መኪናዎች ቁጥር እየተበራከተ መምጣቱን ተከትሎ በሀገር ውስጥ ስላሉት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ምን ዕቅድ እንዳለው መንግስት አላሳወቀም። [ዋዜማ]

The post መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ የግል ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ሙሉ በሙሉ አገደ first appeared on Wazemaradio.

The post መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ የግል ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ሙሉ በሙሉ አገደ appeared first on Wazemaradio.

[…]

Ethiopia Commodity Exchange (ECX) Daily Trade Data – 20 March 2024

ECX Logo

Here is the daily commodity trade data from Ethiopia Commodity Exchange (ECX) for items traded on 20 March 2024.

[…]

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.