Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

የኢትዮጵያ ራዲዮ እና ቴሌቭዥን ድርጅት በአዲስ መልክ ሊዋቀር ነው

ዋዜማ ራዲዮ- የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞው “የኢትዮጵያ ራዲዮ እና ቴሌቭዥን ድርጅት” በአዲስ መልክ ሊዋቀር ነው። አዲሱ አወቃቀር የሀገሪቱ የፖለቲካ ሁኔታ መቀየሩን ተከትሎ ሀገራዊ አንድነትን የሚፈታተኑ ተግዳሮቾችን ለመቀልበስ ያለመ ነው ተብሏል።
በአዲሱ አደረጃጀት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሚለው ስያሜ “የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን” ወደሚለው የቀድሞ ስያሜው ይመለሳል።
ምክንያቱ ደግሞ ተቋሙን ብዙ ሰው የሚያውቀው በዚህ ስያሜ ስለሆነ የሚል ነው።
የራዲዮና የቴሌቭዥን ዘርፉ እንዲለያዩ የሚደረግ ሲሆን የጋዜጠኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች ምደባና ቅጥር ይደረጋል። የሚሰናበቱ ሰራተኞችም ይኖራሉ።

አሁን በአንድ ሥራ አስኪያጅ የሚመሩት ሁለቱ ተቋማት የየራሳቸው አስተዳደር ይኖራቸዋል።
የራዲዮና የቴሌቭዥን ዘርፉ እንዲዋሀዱ የተደረገው 2001 ዓም ነበር።
በአዲሱ መዋቅር የቴሌቭዥኑ አንደኛ ጣቢያ ዜና፣ ሁለተኛው መዝናኛ ሶስተኛው ደግሞ የተለያዩ ቋንቋዎች እንዲሰራጩበት እንደሚደረግ እቅድ ወጥቷል።

የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቭዥን ባለፉት አስራ ሁለት አመታት ከገዥው ፓርቲ በተመለመሉ ካድሬዎች በመሞላቱ ከፍ ያለ የፓርቲዎች መቆራቆሻ መድረክ ሆኖ ቆይቷል።
በቅርብ በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች መካከል የተከሰተውን መከፋፈል ተከትሎ በኢቢሲ ውስጥ እየታየ ያለው የፖለቲካ ሽኩቻ ስራ መስራት ከማይቸልበት ደረጃ ደርሷል ይላሉ አስተያየታቸውን ለዋዜማ የሰጡ ሰራተኞች። [ተጨማሪ መረጃና ዝርዝሩን ከግርጌ የድምፅ ዘገባውን ይመልከቱት]

The post የኢትዮጵያ ራዲዮ እና ቴሌቭዥን ድርጅት በአዲስ መልክ ሊዋቀር ነው appeared first on Wazemaradio.

Source:: http://wazemaradio.com/%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB-%E1%88%AB%E1%8B%B2%E1%8B%AE-%E1%8A%A5%E1%8A%93-%E1%89%B4%E1%88%8C%E1%89%AD%E1%8B%A5%E1%8A%95-%E1%8B%B5%E1%88%AD%E1%8C%85%E1%89%B5-%E1%89%A0/

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.