Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

ESAT Eletawi የህወሓት ጥሪ፣ መከላከያ ሠራዊቱ እና ቀጣዩ ሁኔታ Monday 26 Oct 2020

[…]

Ethiopia: Training on New Portal for MSE's Conducted

Ebiz Online Solutions PLC – the company behind the popular Ethiopian business portal, 2merkato – is conducting a training for officials of the Bureau of Job Creation and Enterprise Development (BoJCED) from 116 woredas in Addis Ababa.

[…]

ESAT Eletawi የጉራፈርዳ የነዋሪው ስጋትና ለትራምፕ የኢትዮጵያ ምላሽ Saturday 24 Oct 2020

[…]

ESAT Special Program የፕሬዝዳንት ትራምፕ ማስፈራሪያ Oct 2020

[…]

ESAT Eletawi የአዲስ አበባ ቋንቋ እና የጉራፈርዳ ግድያ Fri 23 Oct 2020

[…]

Ethiopia – ESAT Oduu Afaan Oromoo Jimaata 23 Oct 2020

[…]

Ethiopia – ESAT Tigrigna News Fri 23 Oct 2020

[…]

የገንዘብ አስቀማጮች የመድን ፈንድ ሊቋቋም ነው

Addis Ababa, Ethiopia: office buildings in the central business district – photo by M.Torres

ዋዜማ ራዲዮ- የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ አስቀማጮች የመድን ፈንድ (Deposit insurance fund) ሊያቋቁም እንደሆነ ገልጿል። ለኢትዮጵያ በአይነቱ አዲስ የሆነው ተቋምን ለማቋቋምም የህግ ሰነዶች መዘጋጀታቸውን የብሄራዊ ባንኩ ገዥ ይናገር ደሴ (ዶ/ር ) ከሰሞኑ በሰጡት መግለጫ አንስተዋል።

የገንዘብ አስቀማጮች የመድን ፈንድ ባንኮችን ለአደጋ የሚዳርግ የገንዘብ ቀውስ በሚፈጠርበት ጊዜ ገንዘባቸውን በባንክ ያስቀመጡ ቆጣቢዎች ገንዘባቸውን እንዳያጡ የሚረዳ የመድን ተቋም ነው።

ይህ ተቋም ለገንዘብ አስቀማጮች ደህንነት ሲባልም ከባንኮች ለአስቀማጮቻቸው የቁጠባ ዋስትና እንዲሆን አረቦን የሚቀበል ይሆናል።መሰል ተቋማት ለሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ጤናማነት ዋስትና የሚሰጡ ናቸው። እስካሁን ባለው አሰራር የኢትዮጵያ ባንኮች ከባድ አደጋ ውስጥ ቢወድቁ የገንዘብ አስቀማጮች እጣ ፈንታ ምን እንደሚሆን በአስተማማኝ የተመለሰበት ሁኔታ የለም።

የገንዘብ አስቀማጮች የመድን ፈንድን የሚያቋቁመው የህግ ሰነድ በጠቅላይ አቃቤ ህግ አስተያየት አልፎና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆም የፈንድ ተቋሙ ወደ ስራ እንደሚገባም ይጠበቃል።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ከ2013 አ.ም በጀት አመት የመጀመርያ ሶስት ወራት ለውጭ ከተላኩ ምርቶች 832 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘቷን ከብሄራዊ ባንኩ የተገኘ መረጃ ያሳያል። ከወጪ ንግድ የተገኘው የውጭ ምንዛሬ ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ15 በመቶ እድገት አሳይቷል። ለዚህም ከወርቅ የተገኘው ምንዛሬ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ የመግዣ ዋጋውን ከፍ ካደረገ በኃላ የሚቀርብለት የወርቅ መጠን መጨመሩን የባንኩ ገዥ ይናገር ደሴ (ዶክተር) ገልጸዋል፡፡

የባንኩ ገዥ ከዚህ ቀደም እንደገለጹት ብሄራዊ ባንኩ ወርቅን ከአቅራቢዎች የሚገዛበት ዋጋ ላይ የመቶኛ ጭማሬ በማድረጉ የሚቀርብለት ወርቅ ከጎረቤት ሀገራትም የመጣ ሳይሆን እንዳልቀረ የሚያስጠረጥሩ ምልክቶች ታይተዋል። በሌላ በኩል የኮሮና ቫይረስ ሲከሰት ኢትዮጵያ የየብስ ድንበሮቿን ስለዘጋች ወርቅ በኮንትሮባንድ ከሀገሪቱ የሚወጣበትን መንገድ ዘግቶት መቆየቱም ከወርቅ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ አሳድጎታል።

ለገቢ ሸቀጦችም በሶስቱ ወራት 3.5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላርን ኢትዮጵያ ወጪ ያደረገች ሲሆን ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲታይ በሰባት በመቶ ቅናሽ አሳይቷል፡፡ቢሆንም ግን የንግድ ሚዛን መዛነፉ አሁንም ከመስተካከል ርቆ ለመገኘቱ ማሳያ ነው።

መንግስት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወጪውን ለመሸፈን እንደ ዋነኛ አማራጭ ከወሰደው የግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ ወደ 33.46 ቢሊየን ብር በሦስት ወራት ውስጥ ሰብስቧል ብሏል ብሄራዊ ባንኩ።

የግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭን እንደ አዲስ ለማስጀመር ሲወጠን በገበያ እንዲመራ በማድረግና ባንኮችን ጨምሮ ብዙ ተቋማት እንዲሳተፉበት መደረጉ በቂ ሀብት ለመሰብሰብ እንዳስቻለም ብሄራዊ ባንኩ ገልጿል። ከዚህ ቀደም መንግስት ወጪውን ለመሸፈን ብሄራዊ ባንኩን ገንዘብ እንዲያትም በሚደርግ መልኩ መሆኑ በሀገሪቱ የዋጋ ንረት በማስከተሉ በገበያ ውስጥ ያለውን ገንዘብ ዋጋ ንረት ፈጣሪ ባልሆነ መልኩ መጠቀም ያስችላል ተብሎ የታመነበት የግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ በአዲስ መልክ ባለፈው አመት ተጀምሯል።

ባንኮች 55 ቢሊየን ብር ብድርን ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ያቀረቡ ሲሆን አብዛኛው ብድርም ለግሉ ዘርፍ የቀረበ መሆኑም በብሄራዊ ባንኩ ገዥ ይናገር ደሴ ተገልጿል።

በኢትዮጵያ አንድን ተበዳሪ ስንት ባንክ ላይ ብድር እንደወሰደ እና ሌሎች የተበዳሪ መረጃዎችን ለማግኘት እና ለማወቅ አስቸጋሪ ነው ; ብዙ መረጃ ክፍተቶችም የነበሩበት ነው፡፡ ይህንን ክፍተት ለመሙላት የክሬዲት ሪፈረንስ ቢሮ ተቋቁሞ የብድር መረጃ አገልግሎት በመስጠት ባንኮች ሰለደንበኞቻቸው የብድር ታሪክ እና ተጋላጭነት የተሻለ መረጃ እንዲኖራቸውና በዕውቀት ላይ የተመሰረተ የብድር ትንተና እንዲሰሩ አሰራር ተዘርግቷል። እስካሁን ከ3 ሚሊዮን በላይ የተበዳሪዎች መረጃ በክሬዲት ሪፈረንስ ቢሮ የመረጃ ቋት ውስጥ እንዲካተት ተደርጓል።

በኢትዮጵያ እያደገ በመጣው የባንክ ዘርፍ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች እጥረት ስላለ ይህንን እጥረት ለመቅረፍ እንዲያስችል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በኩል አቃቂ የሚገኘውን የፋይናንስ ስልጠና አካዳሚ በአዲስ መልክ እንዲቋቋም ደንብ ተዘጋጅቶለታል ተብሏል። በቅርቡ በሚንስትሮች ምክርቤት ከፀደቀ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። የስልጠና ማዕከሉ ለመንግስት እና ለግል ባንኮች ለፋይናንስ ተቋማት፣ ለኢንሹራንስ ሰራተኞች ስልጠና ይሰጣል። በተለይም አሁን ላይ ከወለድ ነፃ አገልግሎት የሚሰጡ ባንኮች ላይ ከፍተኛ የባለሙያዎች እጥረት ስላለ ይህንን ለመቅረፍ ባንኮች ከሚሰጡት አጫጭር ስልጠና በተጨማሪ ስልጠና ማእከሉ ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ተስፋ ተደርጓል፡፡ [ዋዜማ ራዲዮ]

The post የገንዘብ አስቀማጮች የመድን ፈንድ ሊቋቋም ነው appeared first on Wazemaradio.

[…]

ESAT Eletawi የፌደሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ተፈጻሚነት እና የኢሳት ወደ አየር መመለስ Thurs 22 Oct 2020

[…]

አቃቤ ህግ በእነ እስክንድር ነጋ ጉዳይ ምስክሮች በዝግ ችሎትና ከመጋረጃ በስተጀርባ ሆነው ይሰሙልኝ አለ። ጉዳዩ ክርክር አስነስቷል

በዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ አቃቤ ህግ በእነ እስክንድር ነጋ ጉዳይ ምስክሮች በዝግ ችሎትና ከመጋረጃ በስተጀርባ ሆነው ይሰሙልኝ በማለት ያቀረበው አቤቱታ ከፍታኛ ተቃውሞ እና ክርክር አስነስቷል፡፡ የዋዜማ ሪፖርተር ጉዳዩን ተከታትላዋለች

ዋዜማ ራዲዮ- የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ብሄርና ሀይማኖትን መሰረት ያደረገ ገጭት እንዲፈጠር በማነሳሳትና መንግስትን በማዳከም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስልጣንን በሀይል ለመያዝ እንዲሁም የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ሞት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በኦሮሞ እና በትግራይ ተወላጆች ላይ እንዲሁም በእስልምና ምነት ተከታዮች ላይ ጥቃት እንዲፈፀም ትዕዛዝ ሰጥተዋል ባላቸው 7 ግለሰቦች ላይ የሽብር ወንጀል ክስ መመስረቱ ይታወሳል፡፡

በዚህ የክስ መዝገብ ላይ የተካተቱት እና በማረሚያ ቤት የሚገኙት አቶ እስክንድር ነጋ፣ ስንታየሁ ቸኮል፣ ቀለብ ስዩም እና አስካለ ደምሌ ሲሆኑ ጌትነት በቀለ ደግሞ የዋስትና መብቱ ተከብሮ ጉዳዩን በውጭ እየተከራከረ ይገኛል፡፡ ቀሪ 2 ተከሳሾች ደግሞ እስካሁን በፖሊስ ቁጥጥር ስር አልዋሉም ፡፡

ይህን መዝገብ ለመመልከት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ በህገመንግስት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች እና የፀረሽብር ወንጀል ችሎት ዛሬ ጥቅምት 12ቀን 2013 ዓም ረፋድ ላይ ተሰይሟል፡፡

በዛሬው ችሎት አቃቤ ህግ በዚህ መዝገገብ ላይ የሚቀርቡ ምስክሮች በዝግ ችሎትና ከመጋረጃ በስተጀርባ ሆነው ይሰሙልኝ በማለት ያቀረበው አቤቱታ ከፍታኛ ተቃውሞ እና ክርክር አስነስቷል፡፡

“የተፈፀመው ወንጀል ሀይማኖት እና ብሄርን መሰረት ያደረገ እና ለሀገር ደህንነት አደጋ የሆነ የሽብር ወንጀል ነው” ያለው አቃቤ ህግ “ምስክሮቹ ከተከሳሾች ጋር ጥብቅ ግንኙነት ያላቸው በመሆኑ ለጥቃት ይጋለጣሉ እንዲሁም በቀዳሚ ምርምራ ምስክር ማሰማት ሂደት ላይ የግድያ ዛቻ እንደደረሰባቸው የገለፁልን ምስክሮች በመኖራቸው በአዋጅ ቁጥር 699/2003 መሰረት ለምስክሮቻችን ጥበቃ ይደረግላቸው” በማለት አቤቱታ አቅርቧል፡፡

“ይህ የተከሳሾችን ፍትህ የማግኘት መብት አያጠብም” ያለው አቃቤ ህጉ እንዲሁ “እናቅርብ ቢባል እንኳ ምስክሮቻችን ጥበቃ ካልተደረገላቸው ቀርበው ለመመስከር ፍቃደኛ አይሆኑም” በማለት ተናግሯል፡፡

ተከሳሾች እና እና ጠበቆቻቸውም በዚህ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ አንስተዋል፡፡

ሰፊ ዝርዝር የያዘ ተቃውሞ በችሎት ያሰማው 1ኛ ተከሳሽ ሆኖ የቀረበው አቶ እስክንድር በበኩሉ በቀይ ሽብር ወንጀል ተከሰው የነበሩ ተከሳሾችን እንደ አብነት በማንሳት ተቃውሞውን ጀምሯል፡፡

“በቀይሽብር ወንጀል በተከሰሱት ተከሳሾች እንኳን ምስክር ከመጋረጃ ጀርባ እንዲሆን አልተጠየቀም ነበር፤ እነዛ ተከሳሾች የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው ሲወጡ ከመሰከረባቸው ማህበረሰብ ጋር ተቀላቅለው ነው ኑሯቸውን የቀጠሉት ይህ ደግሞ በኢትዮጵያ ምስክሮችን የመበቀል ባህል እንደሌለ ማሳያ ነው” ብሏል፡፡

አቶ እስክንድር አክሎም ይህ ክስ የተመሰረተ እለት አቃቤ ህግ ሙሉ ሂደቱን በግልፅ ችሎት ነው መደረግ ያለበት ማለቱን በማስታወስ ችሎቱ ምስክር ማስማት ሂደቱ በግልፅ ችሎት እንዲያደርግ ጠይቋል ፡፡

ይህ የማይሆን ከሆነ ደግሞ የመገናኛ ብዙሃን የምስክሮችን ዝርዝር ቃል እዳየይገልፁ የተጣለው ገደብ ተነስቶላቸው ሂደቱን ሙሉ ለሙሉ በድምፅ መከታተል እንዲችሉ እንዲፈቀድ አማራጭ ሀሳቡን አቅርቧል፡፡

“የህጎች ሁሉ የበላይ የሆነው ህገመንግስቱ ተከሳሾች ምስክሮቻቸውን የማየት መብት እንዳለቸው እየደነገገ በዝግ ችሎት እና ከመጋረጃ ጀርባ ማድረጉ ይጣረሳል” በማለት ተቃውሞ ያቀረቡት ደግሞ 3ኛ ተከሳሽ የሆኑት ወይዘሮ ቀለብ ናቸው፡፡

ወ/ሮ ቀለብ አክለውም “ለአቃቤ ህግ ይሄ የሚፈቀድ ከሆነ መከላከል ደረጃ ላይ ስደርስ እኔም የመከላከያ ምስክሮቼን ከመጋረጃ ጀርባ እንዳሰማ ይፈቀድልኛል ወይ?” ሲሉ ችሎቱን ጠይቀዋል፡፡

ከአንደኛ እስከ አራተኛ ላሉት ተከሳሾች ወክለው የቀረቡት ጠበቆች በበኩላቸው ተከሳሾቹ በተነናገሩት የተቃውሞ ሀሳብ ላይ ሞያዊ ድጋፋቸውን እንዲህ ሲሉ አቅርበዋል፡-

“አቃቤ ህግ በአቤቱታው ምስክሮቼ ከተከሳሾቹ ጋር ስለሚተዋወቁ ሲል ገልጿል የሚተዋወቁ ከሆነ ደግሞ ከመጋረጃ ጀርባ ማድረጉ ምን ፋይዳ አለው? ከዚህ በተቃራኒው እንደውም የመስቀለኛ ጥያቄ ስናቀርብ እኛን የሚጎዳን ነገር ነው ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አቃቤ ህግ ምስክሮቹ የግድያ ዛቻ ደረሰብን አሉ ብሎ ተናገረ እንጂ ዛቻ እንደደረሰባቸው የሚያሳይ ማስረጃ በችሎት ካቀረበው አቤቱታ ጋር አላያያዘም ይሄ ትልቅ ጥያቄ ነው፡፡ በምስክር ጥበቃ አዋጁ ውስጥ የተዘረዘሩ 20 አይነት የምስክር ጥበቃዎች ቢኖሩም ከእነዛ ውስጥ ከባዱን መምረጡ ሆን ተብሎ እና የፍትህ ስርዓቱን አዳጋች ለማድረግ ነው” ብለዋል፡፡

በዋስትና ጉዳዩን ከውጭ ሆኖ የሚከራከረውን 5ኛ ተከሳሽን ወክለው የቀረቡት ጠበቆች በበኩላቸው ደግሞ ባቀረቡት የተቃውሞ ሀሳብ

“የምስክር ጥበቃ አዋጁ ላይ አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 3 ላይ በተቀመጠው መሰረት የምስክር ጥበቃ እንዲደረግለት ከፈለገ ምስክሩ እራሱ ማመልከቻ ማቅረብ ይኖርበታል ያን ማድረግ የማይችል ከሆነ ፖሊስ ወይም አቃቤ ህግ ያቀርበለታል ነው የሚለው ነገር ግን በዚህ ሁኔታ ምስክሮቹ ማልከቻ ማቅረብ ስላለመቻላቸው የቀረበም ሆነ የተያያዘ ነገር የለም፡፡” ብለዋል

አክለውም “ለመስቀለኛ ጥያቄ እንዲረዳ ምስክሩ አካላዊ ብቃቱ ምን ሁኔታ ላይ ነው የሚለውን ተከሳሾችም ሆነ ጠበቆች ማረጋጋጥ መብት አላቸው ለእነሱ ብቻ ሳይሆን በችሎቱም ያ ሊረጋገጥ ይገባል፡፡ ለምሳሌ ያክል እንዲህ ሲያደርጉ አይቻለው ብሎ ከመጋረጃ ጀርባ ሆኖ የሚመሰክረው ምስክር እውነትም ማየት ይችላል ወይ የሚለውን ማረጋገጥ መቻል አለብን፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ደግሞ የመስቀለኛ ጥያቄ ሲደረግ መስካሪው በሚናገርበት ወቅት የሚያደርጋቸውን አካለዊ እንቅስቃሴዎችንም መሰረት ተደርጎ ነው:: የአፍ ፣ የእጅ እና የእግር እንቅስቃሴ መስካሪው እየዋሸ ነው ወይ የሚለውን ለመመለየት እና መስቀለኛ ጥያቄዎችን ለማቅረብ ይረዳናል ፡፡ ይህም ሁሉ እንዳለ ሆኖ ደግሞ መስካሪው ከዚህ በፊት በሀሰተኛ ምስክርነት ወንጀል እንደሌለበት ልናረጋግጥ ይገባል፣ ከመጋረጃ ጀርባ ወረቀት እያነነበበ እንደማይመሰክር ምን ማረጋገጫ አለን ፍርድ ቤቱን ብናምነውም ከጀርባ የሚሰራው ስራ ግን አመኔታው ጥያቄ ውስጥ ሊገባ የሚችል ነው ፡፡” በማለት ከፍተኛ ተቃውሞ አንስተዋል፡፡

አቃቤ ህግ ለቀረበው ተቃውሞ የመልስ መልስ ለመስጠጥ እድል እንዲሰጠው ችሎቱን ቢጠይቅም ችሎቱ ግን አቤቱታችሁን በዝርዝር ማቅረብ ትችሉ ነበር አሁን የመልስ መልስ ለመስጠት እድል አንሰጥም በማለት ከልክሏል፡፡

በዛሬው ዕለት በተጨማሪም በቀረበባቸው ክስ ላይ ከ1-4 ያሉት ተከሳሾች ከዚህ ቀደም ባቀረቡት የመጀመርያ ደረጃ የክስ መቃወምያ ላይ አቃቤ ህግ በጸሁፍ ምላሽኑ ለችሎት አስገበቷል፡፡

የግራ ቀኙን ክርክር ሲያደምጥ የቆየው ችሎቱ በስተመጨረሻም ትዕዛዞቹን አስተላልፏል፡፡

በዚህም ፖሊስ 6ኛ እና 7ኛ ተከሰሾችን ፈልጎ ያላቀረበበትን ወይንም የደረሰበትን ደረጃ ያላሳወቀበት ምክኒያት የፖሊስ ሀላፊው ቀርበው በቀጣይ ቀጠሮ እንዲያብራሩ እንዲሁም ዛሬ በተደረገው ክርክር እና በመቃወምያውን መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለህዳር 29 ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡

ተከሳሾቹ ለምርጫ መዘጋጀት ስላለብን የቀጠሮ ቀን አይራዘምብን በማለት ጥያቄ ቢያቀርቡም ችሎቱ ትዕዛዙን አፅንቷል፡፡ [ዋዜማ ራዲዮ]

The post አቃቤ ህግ በእነ እስክንድር ነጋ ጉዳይ ምስክሮች በዝግ ችሎትና ከመጋረጃ በስተጀርባ ሆነው ይሰሙልኝ አለ። ጉዳዩ ክርክር አስነስቷል appeared first on Wazemaradio.

[…]

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.