Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

PepsiCo Interesting in Investing in Ethiopia

Pepsico

The American multinational food, snack and beverage corporation PepsiCo Inc. has expressed interest to invest in Ethiopia. Shiferaw Teklemariam (Ph.D.), Ethiopia’s Ambassador to South Africa, has held a discussion with senior management of PepsiCo’s African branch.

[…]

Ethiopia Prepares to Privatize 10 Sugar Factories

sugar

Ethiopia’s Ministry of Finance announced that preparations are underway to privatize ten sugar factories. This will be done in a way that will be of benefit to the country, the Ministry emphasized.

[…]

Ethiopia – ESAT Amharic Day Time News Wed 28 Oct 2020

[…]

Ethiopia – ESAT Oduu Afaan Oromoo Kibxata 27 October 2020

[…]

Ethiopia – ESAT Amharic News Tues 27 Oct 2020

[…]

Ethiopian Airlines Named Best African Airline 2020

Best African Airline

Ethiopian Airlines has been named Best African Airline by Business Traveller Awards 2020. The award, unveiled by the publishers of Panacea Media’s Business Traveller magazine, are voted for by readers of the magazine.

[…]

ESAT Eletawi የአብን ሰልፍ መከልከል! Tue 27 Oct 2020

[…]

በጠቅላይ ሚኒስትሩ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ቦምብ በማፈንዳት የተከሰሱት 5 ግለሰቦች ላይ ፍርድ ተሰጠ

ዋዜማ ራዲዮ- የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ለመደገፍ በተደረገው ሰልፍ ላይ የደረሰውን የቦምብ ፍንዳታ ተከትሎ ለጠፋው የ2 ሰዎች ህይወት እና በ150 ሰዎች ላይ ለደረሰው ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ተጠያቂ ናቸው ያላቸው 5 ግለሰቦች ላይ ወንጀለኛ መቅጫ ህግ እና በሽብር ወንጀል አዋጁ ክስ መመስረቱ ይታወሳል፡፡

በድርጊቱ ላይ እጃችው አለበት የተባሉት ተከሳሾች ጌቱ ግርማ፣ ብርሀኑ ጁፋር ፣ ጥላሁን ጌታቸው ፣ ባህሩ ቶላ እና ደሳለኝ ተስፋዬ ክርክራቸውን በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የፀረ ሽብር እና ህገመንግስት ጉዳዮች ችሎት ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡

የግራ ቀኙን ክርክር ሲመረምር የቆየው ችሎቱ ዛሬ የቅጣት ውሳኔ ለማስተላለፍ ረፋድ ላይ ተሰይሞ ነበር፡፡

በዚህም ድርጊቱ የተፈፀመው የሀገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ለመግደል መሆኑ እና በወቅቱ ተገድለው ቢሆን ኖሮ በሀገሪቱ ላይ ሊደርስ የሚችለውን ከፍተኛ የሰላም መደፍረስ እንደ ቅጣት ማክበጃ እንዲወሰድለት አቃቤ ህግ ያቀረበውን ጥያቄ ችሎቱ ከግምት ውስጥ አስገብቷል፡፡

በሌላ ጎን ተከሳሾችም የየራሳቸውን የቅጣት ማቅለያ ለችሎቱ አስገብተዋል፡፡፡

በዚህም መሰረት ከዚህ በፊት የወንጀል ሪከርድ የለብንም እንዲሁም የቤተሰብ አስተዳዳሪ ነን በማለት የቅጣት ማቅለያ ያስገቡት ጌቱ ግርማ እና ብርሀኑ ጁፋር በ23 አመት እና በ22 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ችሎቱ ወስኗል፡፡

በእለቱ ቦምብ በመወርወር ለ2 ሰዎች ህይወት ማለፍ እና 150 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት እንዲደርስ የወንጀል ድርጊቱን በቀጥታ ፈፅሟል የተባለው ጥላሁን ጌታቸው ደግሞ ምንም አይነት የቅጣት ማቅለያ ያላቀረበ ሲሆን ችሎቱም የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወስኖበታል፡፡

በእለቱ ሁለተኛውን ቦምብ ቢወረውርም ምንም ጉዳት አላደረሰም የተባለው ባህሩ ቶላ ደግሞ በ17 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ችሎቱ ወስኗ፡፡

በመጨረሻም ስለታቀደው የሽብር አላማ እና ወንጀል መረጃው እያለው ለፖሊስ ባለማሳወቅ የወንጀሉ ተባባሪ ሆኗል የተባለው 5ኛ ተከሳሽ ደሳለኝ ተስፋዬ ደግሞ በ5 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኗል፡፡

ታራሚዎቹ የችሎቱ የቅጣት ውሳኔ ከተሰማ በኋላ በጭብጨባ የተቀበሉ ቢሆንም የፍርድ አሰጣጡን ግን አግባብ አይደለም ሌብነት ነው በማለት ተቃውሞ እያሰሙ ከችሎት ወጥተዋል፡፡ [ዋዜማ ራዲዮ]

The post በጠቅላይ ሚኒስትሩ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ቦምብ በማፈንዳት የተከሰሱት 5 ግለሰቦች ላይ ፍርድ ተሰጠ appeared first on Wazemaradio.

[…]

ESAT Tikuret የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ወቅታዊ ችግሮች Oct 2020

[…]

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተከራያቸው 560 አውቶብሶች የግልጽነትና አዋጭነት ጥያቄ እየተነሳባቸው ነው

ዋዜማ ራዲዮ- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን የትራንስፖርት ችግር ይፈታሉ በሚል የተከራያቸው 560 አውቶብሶች ጉዳይ የአዋጭነትና የግልፅነት ጥያቄዎች እየቀረበበት ነው። አስተዳደሩ ግን የከተማዋን የትራንስፖርት መፍታት ቀዳሚ አጀንዳው መሆኑን ይገልፃል። ።

ዋዜማ ራዲዮ እንደተረዳችው ከሆነ አውቶብሶችን ተከራይቶ ለከተማዋ ትራንስፖርት አገልግሎት የማዋሉን ነገር አስበው ወደ ተግባር ሊገቡ የነበሩት የቀድሞው የከተማዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ ነበሩ። ሆኖም በወቅቱ ከተለያዩ አካላት ጋር በተደረገ ውይይት “አውቶብስ መከራየቱ አያዋጣም” የሚል አስተያየት ስለበዛ እንዲቀር ተደርጎ ነበር። የአሁኗ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ግን ከጥቅምት 9 2013 አ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባን የትራንስፖርት ችግር ያቃልላል በሚል በፍጥነት የአውቶቡስ ኪራይ ዕቅዱን ተግባራዊ አድርገውታል።

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለተከራያቸው 560 አውቶብሶች ጨረታ እንዳላወጣ ዋዜማ ራዲዮ አረጋግጣለች። የኪራዩ አካሄድ በጨረታ ማለፉ በአንጻሩም ግልጽነትን ሊያመጣ ቢችልም በምን መልኩ አውቶብሶቹ እንደተመረጡም ግልጽ አይደለም። የመስተዳድሩ ሀላፊዎች ከአውቶብሶቹ ባለቤቶች ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገው ከዚያም እንደ አውቶብሶቹ ሁኔታ ወርሀዊ የኪራይ ሂሳብ ወጥቶላቸው ከከተማዋ የትራንስፖርት ቢሮ ጋር ውልን እንደተዋዋሉ ያሰባሰብነው መረጃ ያመለክታል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተከራያቸው አውቶብሶች በብዛት የክፍለ ሀገር መጓጓዣ የነበሩ ናቸው። አሁን በኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች የጸጥታ ሁኔታ አስተማማኝ ስላልሆነ እንዲሁም በኮሮና ቫይረስ ምክንያት አውቶብሶቹ የአገልግሎት ገደብም ስላለባቸው በከተማው መሰማራታቸው ለህልውናቸው መቀጠል ደጋፊ እርምጃ መሆኑን የመስተዳድሩ ምንጮቻችን ይናገራሉ። ነገር ግን አውቶብሶችን የመከራየቱ ነገር የከተማ አስተዳደሩን ለገንዘብ ብክነት የሚዳርግ እና መከራት አስፈላጊ ቢሆን እንኳ ሌሎች የተሻሉ መንገዶች እንደነበሩ በሂደቱ የተሳተፉት የመረጃ ምንጮች ያሰምሩበታል።

የከተማ አስተዳደሩ ለ560ዎቹ አውቶብሶቹ ኪራይ በወር 71 ሚሊየን ብር ያወጣል። እንደተባለው የአውቶብሶቹ ኪራይ ለስድስት ወራት ብቻ የሚቆይ ቢሆን እንኳ የከተማ አስተዳደሩ ለአውቶብሶቹ ኪራይ ለስድስት ወራት 426 ሚሊየን ብር ወጪ ይጠብቀዋል። ይህን ያክል መጠን ያለውን ገንዘብ ለኪራይ ከማውጣት እስከ 100 የሚደርሱ አውቶብሶችን መግዛት አይሻልም ነበር ወይ ? የሚል ጥያቄን አስነስቷል። የከተማ አስተዳደሩ በቢሊየን በሚቆጠር ገንዘብ ሶስት ሺህ አውቶብሶችን ለመግዛት እየተዘጋጀ መሆኑን በቅርቡ ወራት አስታውቋል። ታዲያ ስለምን ከፍ ያለ ኪራይ ወደሚያስወጣ ኪራይ መሄድን እንደመረጠ አሳማኝ ምክንያት አልቀረበም። መስተዳድሩ በጉዳዩ ላይ ሀሳብ እንዲሰጥ ለማግባባት ብንሞክርም ከምክትል ከንቲባዋ በቀር በዚህ ጉዳይ መናገር የሚችል የለም በሚል ምክንያት የተብራራ ምላሽ አላገኘንም።

ዋዜማ ራዲዮ ከምንጮቿ እንደሰማችው ከሆነ በኪራይ ወደ ስራ ገቡ የተባሉት አውቶብሶች እንደየደረጃቸው በአንበሳ አውቶብስና በሸገር ባስ ታሪፍ ተሳፋሪዎችን እያስከፈሉ ይሰሩና በኪራይ አገልግሎቱን ስለሰጡ ብቻ ከከተማ አስተዳደሩ እንደየአውቶብሶቹ ደረጃ ወርሀዊ ኪራይ ይከፈላቸዋል።

የከተማ አስተዳደሩ አውቶብሶቹን በደፈናው ከሚከራይ ይልቅ አውቶብሶቹ ተሳፋሪዎችን ብናስከፍል ያዋጣናል የሚሉት ዋጋ አቅርበው በሱ ላይ ድርድር ከተደረ በሁዋላ የከተማ ትራንስፖርት እንዲሰጡ ቢፈቀድ ; እንዲሁም በአንበሳ አውቶብስና ሸገር ባስ ታሪፍ ሰርተው ህጋዊ ማረጋገጫ አቅርበው በመንግስት ታሪፍ በመስራታቸው ያጋጠማቸውን የገቢ ክፍተት ከተማ አስተዳደሩ ይሙላላቸው የሚሉ አማራጮች የቀረቡ ቢሆንም ተቀባይነት አለማግኘቱን ሰምተናል። [ዋዜማ ራዲዮ]

To reach Wazema Editors write —wazemaradio@gmail.com

The post የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተከራያቸው 560 አውቶብሶች የግልጽነትና አዋጭነት ጥያቄ እየተነሳባቸው ነው appeared first on Wazemaradio.

[…]

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.