Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

የባድመ ጉዳይ

መስፍን ወልደ ማርያም
ሰኔ 2010

የባድመ ጉዳይ ምንጩ የኤርትራ መገንጠል ነው፤ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ስትገነጠል ጎደሎ ሆነች፤ ኢትዮጵያም ጎዶሎ ሆነች፤ የኢትዮጵያና የኤርትራ ጎዶሎነት አንዱ ሌላውን የመፈለግ የተፈጥሮ ግዴታን አመጣ፤ ለሁለት የተከፈለ አንድ ባሕርይ ዘለዓለም ሲፈላለግ ይኖራል፤ ችግሩ ከሰዎቹ ነው፤ የባድመ ጉዳይ የሁለት ጎዶሎ አገሮች አንዱ ሕመም ነው፤መቼ ተጀመረ?

አንዳንድ ሰዎች ስለአልጄርስ ስምምነት ሲገልጹ የመንደር ስምምነት ያስመስሉታል፤ አንደኛ ስምምነቱ የተደረገው በተባበሩት መንግሥታት ጥላ ስር በተባበሩት መንግሥታት የመቋቋሚያ ሰነድ አንቀጽ 102 መሠረት ነው፤ ዋናው አደራጅ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ ሆኖ የተከናወነው በተባበሩት መንግሥታት ጽሕፈት ቤት ውስጥ ነበር፡፡

ሁለተኛ ለስብሰባው በእማኝነት የተገኙትና የፈረሙት የተባበሩት መንግሥት ድርጅት ዋና ጸሐፊ፣ የአውሮፓ ኅብረትና የአፍሪካ ኅብረት ዋና ጸሐፊዎች፣ የአልጂርያ ፕሬዚደንት፤ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናቸው፤ እንግዲህ እንደዚህ ያሉ ከባድ ከባድ እማኖች ተሰልፈውበት በዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የተፈጸመን ስምምነት አሌ ማለት እንዴት ይቻላል? ከተቻለም ሙሶሊንን ወይም ሂትለርን መሆን ነው፡፡

ወያኔ/ኢሕአዴግ ኤርትራን ለማስገንጠል በሚዘጋጅበት ጊዜ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለተቃውሞ ሰልፍ ወጥተው ነበር፤ በ,ያኔ ኢሰብአዊ የጭካኔ ጭፍጨፋ ሰልፉ ተቋረጠ፤ እንግዲህ በኤርትራና በባድመ ጉዳይ ውሳኔዎች በሚሰጡበት ዘመን ትንፋሹን ውጦ እስከዛሬ የቆየ ሕዝብ ዛሬ ከየት ፈልቶ ነው ተቃውሞ የሚያሰማው? ለነገሩ ከአለመኖር ወደመኖር መምጣት ሁሌም የሚያስደስት ነው፤ ትናንት የፈራ ዛሬ ቢደፍርም አያስከፋም፤ ታዝቦ ማለፍ ነው፡፡

Source:: https://mesfinwoldemariam.wordpress.com/2018/06/27/%E1%8B%A8%E1%89%A3%E1%8B%B5%E1%88%98-%E1%8C%89%E1%8B%B3%E1%8B%AD/

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.