Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

በምስራቅ ወለጋ 11 ሰዎች በታጣቂዎች ተገደሉ።

ዋዜማ ራዲዮ- በምስራቅ ወለጋ ኬረሙ ወረዳ ነጭሎ በተባለ አካባቢ አስራ አንድ ሰላማዊ ሰዎች ተገደሉ።

ባለፈው ሀሙስ ዕኩለ ቀን የኦነግ ሼኔ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አስራ አንድ ሰዎች ሲገደሉ ከሀያ በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለዋዜማ ራዲዮ ገልፀዋል።

እስከ ዓርብ ከሰዓት በኋላ ድረስ የሟቾቹ አስከሬን አለመነሳቱን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

የኦነግ ሼኔ ታጣቂዎች በድጋሜ ጥቃት ሊያደርሱ ይችላሉ በሚል ነዋሪዎች ቀበሌውን ለቀው እየወጡ መሆኑንም ለዋዜማ ገልፀዋል።

በጉዳዩ ላይ መረጃ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ሀላፊዎች የችግሩን መከሰት አምነው ዝርዝሩን ከመናገር ግን ተቆጥበዋል።

በቅርቡ የመከላከያ ሀይል በኦነግ ሽኔ ታጣቂዎች ላይ የከፈተውን ሰፊ ዘመቻ ተከትሎ ታጣቂዎቹ ይዞታቸውን ለቀው ወደ ሌሎች አካባቢዎች እየሸሹ መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። [ዋዜማ ራዲዮ]

The post በምስራቅ ወለጋ 11 ሰዎች በታጣቂዎች ተገደሉ። appeared first on Wazemaradio.

Source:: http://wazemaradio.com/%E1%89%A0%E1%88%9D%E1%88%B5%E1%88%AB%E1%89%85-%E1%8B%88%E1%88%88%E1%8C%8B-11-%E1%88%B0%E1%8B%8E%E1%89%BD-%E1%89%A0%E1%89%B3%E1%8C%A3%E1%89%82%E1%8B%8E%E1%89%BD-%E1%89%B0%E1%8C%88%E1%8B%B0%E1%88%89/

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.