Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

ደስታዬን ማመቅ አልቻልኩም

ያለንበትን ወቅት ማመን አስቸግሮኛል። ከጥቂት ቀናት በፊት የነበረኝ ግንዛቤ፤ ጠቅልሎ ከኔ ጠፋ። ፍጹም ያልጠበቅሁት ክንውን፤ ገሃድ ሆኖ፤ አይደረግም ያልኩት ተፈጽሞ፤ የሀገራችን የፖለቲካ ሀቅ ተገለባብጦ ሳገኘው፤ ሰውነቴን ዳሰስኩ። የፈለግሁት ሆነ! ብል ስህተትነው። ነገርግን፤ እየተደረገ ባለው ሂደት ያለሁበትን ማመን አቅቶኛል። ደስ ብሎኛል። ሂደቱ መቀጠል አለበት እላለሁ። ደስታዬን ግን ለራሴ አፍኜ መያዝ አልፈልግም። ለዚህም እንኳን ለዚች ቀን እላለሁ። […] […]

Ethiopia: the 6th Hotel Show Africa Launched in Addis Ababa

The 6th hotel show Africa was inaugurated in Addis Ababa, Ethiopia on Thursday. The hotel show is aimed at connecting domestic and global travel market players and hotel operators.

[…]

Ethiopia: the Ministry of Foreign Affairs Establishes Four New Missions

The Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia announced that it had broadened its foreign missions over the already ending fiscal year focusing on business diplomacy. Four new missions were established and one embassy was relocated, the Ministry stated.

[…]

የአዲስ ኢትዮጵያ ብስራት!

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የተመሠረተባቸው አዕማዶች ሁለት ናቸው። እነዚህም ከጎሣ ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ እንስጥ! እና ሁላችንም አብረን ነጻ ካልወጣን ማንም ብቻውን ነጻ ሊሆን አይችልም! የሚሉት ናቸው። እነዚህን ግዙፍ መርሆዎች ተግባራዊ ለማድረግ የሚጠቀምባቸው ስልቶች ደግሞ ዓመጽ፣ ጥላቻ፣ ክፋት፣ ምቀኝነት፣ ዘረኝነት፣ ወገንተኝነት፣ ወዘተ ሳይሆን ሰብዓዊ ዘርን ከልዩነት በጸዳ ጽኑ ፍቅር በማክበር፣ በመውደድና ለሌላው ሰው ከልብ በመነጨ ቅንነት […] […]

France Development Agency to Grant Ethiopia 18 million Euros

France Development Agency (AFD) agreed to grant Ethiopia 18 million Euros in two separate agreements. The first agreement, a 10 million Euros grant, will be used for urban institutional and infrastructure development program (UIIDP), a program which is co-financed by the World Bank and the government of Ethiopia. The UIIDP is targeted at enhancing the capacity and performance of local urban governments.

[…]

U.S. Secretary of Commerce Wilbur Ross, President’s Advisory Council on Doing Business in Africa Set for Fact-finding Mission to Ethiopia

A press release by the US Embassy in Ethiopia on 20 June 2018

U.S. Secretary of Commerce Wilbur Ross announced today that he will lead a delegation from the President’s Advisory Council on Doing Business in Africa (PAC-DBIA) on a fact-finding mission to Ghana later this month. Under Secretary of Commerce for International Trade Gilbert Kaplan will head the delegation on stops in Ethiopia, Kenya and Côte D’Ivoire as well as accompany Secretary Ross in Ghana. These visits provide an opportunity for the delegation to gather insight into market opportunities and challenges faced by U.S. businesses in these fast-growing economies. The PAC-DBIA will use this information to provide President Trump with reliable and actionable recommendations to deepen commercial relationships in these countries.

[…]

ይድረስ ለአዲሳባ፣ ከአዲስ አበባዊ

IMG_1480

[መስፍን ነጋሽ – ለዋዜማ ራዲዮ እንደከተበው]

ክብርት ሆይ!
ለጤናሽ እንደምን ከርመሻል?! በዐይነ ስጋ ከተያየን ብዙ ቅዳሜ ነጎደ፣ ብዙ ጥር አለፈ! ስንት መውሊድ ተከብሮ ስንት ልደት ተቆጠረ! ስንት ጾም ተይዞ ስንት ጾፍ ተፈታ! ስንት ሰው ተይዞ ስንት ሰው ተፈታ! ስንት ሰው ተወልዶ፣ ስንት ሰው አለፈ! ዝርዝሩ ብዙ ነው።
ስለእኔ የምትሰሚውን ባላውቅም፣ ስላቺ እሰማለሁ፣ ስላቺ እሳላለሁ። ስለእኔ ያልሽውን ባላውቅም፣ ስላቺ አነባለሁ፣ ስላቺ አነባለሁ።
ለሁሉም ሰው የበቀለበት ቀዬው እንደሚሆንለት ሁሉ፣ በእኔ የሕይወት ሰሌዳ ላይ የፈሰሰው ኅብረ ቀለም የተቀዳው ካንቺ ነው። ከንባታዎቹ እነማን እንደሆኑ ሳላውቅ፣ በከንባታ ሰፈር እድር ጡሩምባ ከእንቅልፌ ስቀሰቀስ አድጌ፤ በጋሽ ሁሴን አንደበት ተመርቄ፣ ከአባቦና ከፉንጌ እጅ ጎርሼ (ፉንጌ ተሰድጄም ሙልሙል ይልኩልኛል)፤ ከግደይ ጋራ ተምሬ፣ እትዬ ኢትዮጵያ ቤት ተልኬ፤ ከሐረሩ ሰለሞን እንግሊዝኛ፣ ከወለጋው ጋሽ ገለታ ትህትና ተምሬ፤ ከነኬኔዲ ጋራ ጥምቀት ሜዳ ካርታ ተጫውቼ፣ ከነተስፋዬ ጋራ ታቦት አጅቤ፤ ሚስማር ተራ፣ ካታንጋ፣ ግራ ጥላ ለመታደም ታትሬ፤ ካላጣነው ሜዳ ገርጂ አለያም ሾላ ድረስ ለኳስ አራራ ተንከራትቼ፤ አሜሪካ ለሚሄድ ሰው የቤት ውስጥ ፓርቲ ወጥቼ፤ ከ22 መርካቶ የስራፈት ጎረምሳ ወክ አድርጌ፤ የማይገባኝን ፊልም ለማየት ሲኒማ ኢትዮጵያ ተጋፍቼ፣ አቅሜ የማይችለውን መጽሐፍ ገዝቼ፤ እያለ… እያለ… የሰፈራችን ልጅ ጣሃ ሙስሊም አባቱን ለፋሲካ በግ እንዳስገዛ ሰምቼ ስቄ፣ አመንኩ ያልኩ ሰሞን በቴዲ ካሴት ላይ መዝሙር በመቅዳቴ ኋላ በራሴ ስቄ፤ የልጅነት ፍቅረኛዬ ሌላ ስትወድ አይቼ፣ ብሔሯን አላውቅ እንደነበር ካረጀሁ ታዝቤ፤ ሕጻን የነበረችው ለይላ ትልቅ ሰው ሆና ተገርሜ፣ መጎልመሴን ገርምሜ፤ የሆለታ ልጅ ጓደኛ፣ የባህር ዳራ ልጅ ሚዜ ሆኜ፤ ከአዲሳቤው አሉላ ጋራ በአማርኛ ስዋሰው ተጣልቼ፣ የዮሐንስ አድማሱን ግጥሞች በእጄ ገልብጬ ጨርሼ፤ ሰባኪ በነበረ ጊዜ የሚያውቃቸውን ሰዎች ሲያገኝ “ያን ጊዜ ያስተማርኳችሁ ስህተት እንደነበረ ገብቶኛል” ብሎ የሚናዘዘውን የሕሊና ሰው ተዋውቄ፤ አንድ ጊዜ ብቻ ያየኋቸው ሴት አያቴ እየናፈቁኝ፣ አንድ ጊዜ ብቻ ያየኋት የአባቴ ልጅ እየተረሳችኝ፤ እያለ… እያለ…በሕይወቴ እኩሌታ ከታሪክ ጎዳናዎች በአንዱ በድንገት ካገኘኋቸው መንገደኞች ጋራ አዲስ ጨዋታ ገብቼ፣ የሙከራው በረከት ወይም መርገም ካንቺ እስኪለኝ ያለውን ሁሉ የምታውቂው ነው። ከዚያ በኋላ የተኖረው፣ አዲስ ቀለም ባይጠፋበትም መደቡ ግን ያው አንቺ ነሽ፤ አዲስባ። እያለ… እያለ…
የሆነስ ሆነና፣ ሸገር እንደምን ነሽ!

አሁን ቅዳሜ ትልቅ ሕዝባዊ ሰልፍ ለማስተናገድ አስበሻል መባልን ሰማሁ። ሰዉ ሁሉ ደስ ብሎታል አሉ። ሰዉ ደስ ሲለው አንቺንም ደስ እንደሚልሽ አውቃለሁ። ስትስቂም ስታለቅሺም አውቃሻለሁ። ስትፈሪ ስትጨነቂም እናውቅሻለን። እንኳንም ደስ ያለሽ። እንኳንም ተስፋ አደረግሽ።

ሰልፉ አዲሱን መሪ፣ ዐቢይ አህመድን ያዝልቅልህ ለማለት፤ ዴሞክራሲ ይሉትን ውቃቤ ለመለማመን መሆኑን ከልጆችሽ አንደበት ሰማሁ። ከእስራትሽ እየፈታሽ፣ ከስጋትሽ እያወጣሽ ስለሆነ እንዲበረታልሽ ብትመኚ እውነት አለሽ። ልጆችሽን ሲያጎሳቁሏቸው፣ ሲገሏቸው፣ ጣር ሲያበዙባቸው አይተሻልና “እፎይ!” ለማለት ብትቸኩዪ እውነት አለሽ። የግፍ እስረኛ ማጎሪያ አድርገውሽ ሰንብተው፣ ታሳሪዎችሽ ሲፈቱ ብትጨፍሪ፣ ብታለቅሺ እውነት አለሽ፤ ጎድለውብሽ ነበርና። ስደተኞችሽን በዕንባ ብትቀበዪ እውነት አለሽ፣ ጎድለውብሽ ነበርና። አሁንም ያ ቀን እንዳይመለስ ብትመኚ፣ የፍቅርና የይቅርታ እጣን ብታጨሺ፣ እውነት አለሽ።
ማዳመጥን የሚይዳመጥ፣ ልጆችሽ ወደመካ ዞረው የሚሰግዱለት፣ ኢየሩሳሌምን የሚሳለሙለት፣ ዋቃን የሚለምኑበት፣ የየነፍሱ አማልክት ምኞታቸውን እንዲሞሉላቸው ብትመኚ እውነት አለሽ። በጎ ሕሊና ያላቸው ሁሉ፣ አርምሞሽን ይጋራሉ፣ ምኞትሽን ያጸድቃሉ።

እንዲያም ሆኖ፣ ሰልፉ፣ አንዷን ልጅችሽን አስደስቶ ሌላኛዋን የሚያስከፋ እንዳይሆን የሚሰጉ ድምጾች ሰማሁ። ስጋታቸው እንድሚያሰጋሽ አውቃለሁ። ልጆችሽ እንዲህ ያለውን ነገር እንዲጸየፉት አስታውሻቸው። ንገሪያቸው፤ ዘክሪያቸው፤ ገስጻቸው። ያንቺ ልጅነት፣ በአጥንትና በደም ቆጠራ፣ በመወለድ፣ አለዚያም በቋንቋ ጥራት፣ ካልሆነም በሃብት ብዛት የሚገኝ ወይም የሚታጣ እንዳልሆነ አስታውሻቸው። እጅግ ያዘነ፣ የተቆጣ፣ የተቀየመ ወይም የተደሰት ሰው መልካሙን ቀን መርሳት ልማዱ ነውና፣ ደጋግመሽ አስታውሻቸው። ተማጸኛቸው። ይሰሙሻል። ማንም አይከፋ በያቸው።

እንዲያም ሆኖ፣ ግፋቸው ሳያንስ፣ ጉርብትናን ጭምር የሚመርዝ የጥላቻና የመለያየት ዘር ሲበትኑብሽ የሰነበቱ፣ ሰልፉን አስታከው የጠብና የደም አዝመራቸውን ሊሰበስቡ አሰፍስፈው እንደሚጠብቁ ሰማሁ። እውነት ነው? አዲስባ፣ በጉንተላቸው አትዘናጊ፣ በለከፋቸው አትበሳጪ፣ በወጥመዳቸው አትውደቂ። መለያየትና ጥላቻን እምቢ በያቸው። ይመስላቸዋል፤ ይገምታሉ፤ አንቺን በእርስ በርስ ግጭት ውስጥ ከከተቱ፣ መላውን ኢትዮጵያ በተመሳሳይ እሳት እያነደዱ ሊጫወቱበት እንደሚችሉ ያስባሉ። አንቺን የጥላቻና የመለያየት ከተማ በማድረግ፣ ወይም እንዲዚያ ሆናለች የሚል ወሬ በማራባት፣ የኢትዮጵያ ልጆች መሰባሰቢያ መሆንሽን ሊያስቀሩ ይመኛሉ። አንቺን የግጭት መናኸሪያ በማድረግ፣ አብሮ መኖር አይቻልም እያሉ የመለያየት ነጋሪት ከምጎሰም አይመለሱም። በቂ ህመም፣ በቂ ጭንቀት፣ በቂ ሰቆቃ፣ በቂ እሪታ አለብኝ በያቸው። ሲሆን አግባቢያቸው፤ ካልሰሙ በፍቅርና በትዕግስት አሸንፊያቸው።
በቀረውስ አዲሳባ!

የፈረንሳይ ሌጋሲዎኗን ጓደኛዬን እሷ ከእስር ተፈታ፣ እኔ እስር ሸሽቼ ስቶክሆልም ላይ ሳገኛት፤ ከ12 የአዲሳባ ጽዋ ተጣጪዎቼ ስምንቱን አሜሪካ ሳገኛቸው ጭምር ኢትዮጵያን የሚያካልለው የጨዋታችን ባቡር የሚጓዘው ሸገር በሚባል ሐዲድ ላይ እንደነበር ስነግርሽ ምን እንደምትዪ አላውቅም። ያንቺና እኔ መዋደድ ወንጀል ቢሆን ኖሮ፤ ባለቤቴ የገዛችልኝ የስደት ቤታችን አድማቂ ስዕል ፒያሳ አራዳ ፊትለ ፊትን የሚያሳይ መሆኑ የጥፋታችን ማስረጃ ሆኖ በቀረበብን ነበር። የማንክደው ክስ፤ ፍቅራችን።

አውግተን የማንጨርሰው የልብ ጨዋታ አናጣምና ስንገናኝ እንቀጥላለን። ሕልማችንም የጋራ ነውና አብረን እናባዝታለን። አሰፋ ጫቦን፣ ገብሩ መርሻን እና ኢዮብ መኮንንን በመቃብራቸው፣ ምናልባት ካልሞቱ የቄስ ትምህርት ቤት መምህሬን ባሉበት፣ ጋሼ እትዬ እያልኩ የምጠራቸውን ብዙ ሰዎች በያሉበት፣ አንዳንዶቹን አድባራት፣ ብዙዎቹን ጎዳናዎች፣ የሚስቁ የሚያስቁ ጓደኞችን፣ ከአራት ኪሎ ስድስት ኪሎ፣ ስታዲየምንና ብሔራዊን፣ የልጅነት ጥርሶቼ የተበተኑበትን 22 ማዞሪያ፣ ካፌዎቹን እና ሌሎቹንም ታስጎበኚኝ ይሆናል። እስከዚያው ሰላም ሁኚ።

መስፍን ነጋሽ።

The post ይድረስ ለአዲሳባ፣ ከአዲስ አበባዊ appeared first on Wazemaradio.

[…]

ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ ወደ አስመራ ይጓዛሉ

Eritrea's President Isaias Afwerki listens to a question during an interview with Reuters in the capital Asmara May 20, 2009. President Afwerki believes the financial crisis is a welcome restructuring of the global economic order and vindication of Eritrea's much-vaunted principles of self-reliance and sustainability. Picture taken May 20, 2009. REUTERS/

ዋዜማ ራዲዮ- የኢትዮጵያን የኤርትራን ግንኙነት ለማሻሻል በሁለቱም ሀገሮች በኩል ፈቃደኝነት በተገኘበት በአሁኑ ሰዓት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ዝርዝር ጉዳዮችን ለመነጋገር ወደ አስመራ ያቃናሉ ተብሏል።
ዋዜማ ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች እንደሰማችው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በአስመራ ቆይታቸው የድንበር ጉዳይን ጨምሮ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የአለመግባባት ምክንያት ናቸው ተብለው በተለዩ ጉዳዮች ላይ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል። የጠቅላይ ሚንስትሩ ጉብኝት ቀን ይፋ አልተደረገም።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ የኢትዮጵያ ሰራዊት ለኤርትራ እንዲሰጡ በፍርድ ቤት ከተወሰኑ አካባቢዎች በተለይም ከባድመ ለቆ የሚወጣበትንና አጠቃላይ ግንኙነትን ማሻሻል ስለሚቻልባቸው መንገዶች ዝርዝር ይነጋገራሉ ተብሏል።
የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የአልጀርሱን የሰላም ስምምነት ያለቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎ ኤርትራ የልዑክን ቡድን ወደ አዲስ አበባ ለመላክ መወሰኗን አስታውቃለች።

የኤርትራ የልዑካን ቡድን አዲስ አበባ እንደሚገባ እየተጠበቀ ሲሆን በቆይታውም ለጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ የአስመራ ጉብኝት ቅድመ ሁኔታዎችን ያመቻቻል።
እስካሁን ሁለቱ ሀገሮች በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ምንም አይነት ውይይት ያላደረጉ ሲሆን በውይይቱ ልዩነቶቻቸውንም ሆነ ፍላጎታቸውን ያሳውቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ኤርትራ በአዲስ አበባ ለአፍሪቃ ህብረት ተጠሪ ከሆኑ ዲፕሎማቶቿ መካከል አንጋፋውን አምባሳደር አርአያ ደስታን ታሳትፋለች ተብሏል።
ኤርትራ ማናቸውንም ዝርዝር ድርድር ከማድረጓ በፊት የኢትዮጵያ ወታደሮች “ከግዛቴ” መውጣት አለባቸው የሚል ቅድመ ሁኔታ ስታቀርብ መቆየቷ ይታወቃል።
ከሁለቱ ሀገሮች ጀርባ ዩናይትድ ስቴትስ ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትና ሳዑዲ አረቢያ በአግባቢነት ሚና ሲጫወቱ ቆይተዋል።

The post ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ ወደ አስመራ ይጓዛሉ appeared first on Wazemaradio.

[…]

Dawit Gebregziabher on President Isaias Afeworki’s Surprising Announcement to accept Ethiopia’s peace offering call

Awramba Times interviews ato Dawit Gebregziabher on President Isaias Afeworki’s surprising announcement to accept the Ethiopian Government’s peace offering call

[…]

Eritrea sending delegation to Ethiopia for peace talks

Eritrea‘s president announced Wednesday he is sending a rare delegation to neighboring Ethiopia for peace talks, days after Ethiopia’s new prime minister took a major step toward calming deadly tensions with its decades-long rival. This is the first such delegation since 1998, when a border war erupted between the countries and they cut off diplomatic […] […]

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.