Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.

የኦጋዴን ነፃነት ግንባር በኦጋዴን የሚደረገውን የነዳጅ ማውጣት ተቃወመ

Ogaden crude oil inauguration at the presence of PM Abiy Ahmed

Ogaden crude oil inauguration at the presence of PM Abiy Ahmed

ዋዜማ ራዲዮ- የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር በሶማሌ ክልል የተጀመረውን ነዳጅ የማውጣት ፕሮጀክት እንደሚቃወምና የኦጋዴን የራስን ዕድል በራስ መወሰን ሳይረጋገጥ የሚደረግ እንቅስቃሴ ህገ ወጥ ዝርፊያ ነው ብሎ እንደሚያምን አስታወቀ።
የኦጋዴን የነዳጅ ጉድጓድ ተመርቆ የሙከራ ስራ በተጀመረ በሰዓታት ውስጥ ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክቶቹ የክልሉን ህዝብ ጭቆናና የመብት ጥሰት ሊጋርዱት አይገባም ብሏል።

የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር ፕሮጀክቱ ተግባራዊ ከመደረጉ አስቀድሞ የክልሉ የፖለቲካ ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ አለበለዚያ ግን ተግባራዊ መደረጉን አጥብቆ እንደሚቃወም ተናግሯል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ የጀመሩት የፖለቲካ ተሀድሶን በበጎ እንደሚመለከት የገለፀው ድርጅቱ የኦጋዴን የራስን ዕድር በራስ መወሰን መብት እንዲከበር ከዚያም በኦጋዴንና በኢትዮጵያ መንግስት መካከል በሚኖር ስምምነት ብቻ የተፈጥሮ ሀብቱን በፍትሐዊነት መጠቀም ተገቢ ነው ብሎ ያምናል።
ከ 11 ዓመታት በፊት የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር በቻይና የነዳጅ ፍለጋ ስራተኞች ላይ ባደረሰው ጥቃት 63 ኢትዮጵያውያንና 9 ቻይናውያን መገደላቸው ይታወሳል። ይህንን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንግስት በአካባቢው ሚሊሻ በማደራጀትና ሰፊ ወታደራዊ ዘመቻ ከፍቶ ነበር። በድርጊቱም ስፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈፀሙ በተደጋጋሚ ተነግሯል።

The post የኦጋዴን ነፃነት ግንባር በኦጋዴን የሚደረገውን የነዳጅ ማውጣት ተቃወመ appeared first on Wazemaradio.

Source:: http://wazemaradio.com/%E1%8B%A8%E1%8A%A6%E1%8C%8B%E1%8B%B4%E1%8A%95-%E1%8A%90%E1%8D%83%E1%8A%90%E1%89%B5-%E1%8C%8D%E1%8A%95%E1%89%A3%E1%88%AD-%E1%89%A0%E1%8A%A6%E1%8C%8B%E1%8B%B4%E1%8A%95-%E1%8B%A8%E1%88%9A%E1%8B%B0/

Categories

A sample text widget

Etiam pulvinar consectetur dolor sed malesuada. Ut convallis euismod dolor nec pretium. Nunc ut tristique massa.

Nam sodales mi vitae dolor ullamcorper et vulputate enim accumsan. Morbi orci magna, tincidunt vitae molestie nec, molestie at mi. Nulla nulla lorem, suscipit in posuere in, interdum non magna.