Ministry of foreign affairs
አውራምባ ታይምስ (አዲስ አበባ) – የሳውዲ አረቢያ መንግስት የውጡልኝ አዋጅ እንዲራዘም ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ለሳውዲ ንጉስ ሰልማን ቢን አብዱልአዚዝ አል-ሳውድ ኦፊሴላዊ ጥያቄ አቀረቡ ማቅረባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሚኒስቴር መስሪያቤቱ ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት በጠ/ሚኒስትሩ ከቀረበው ጥያቄ በተጨማሪ ሳውዲ በሚገኘው ኢምባሲም ጥያቄው እንደቀረበና የሚሰጠውን ይፋዊ ምላሽ መንግስት እየተጠባበቀ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ቃል አቀባዩ አቶ መለስ አለም ከጋዜጣዊ መግለጫው መጠናቀቅ በኋላ ለአውራምባ ታይምስ በሰጡት አጠር ያለ ቃለመጠይቅ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሌሎች በረራዎችን በመሰረዝና በኪሳራም ጭምር ኢትዮጵያዊያንን እያመላለሰ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ቃል አቀባዩ በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫቸው
ከሳውዲ የውጡልነኝ አዋጅ በተጨማሪ በቅርቡ ስለሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ፣ ስለ ኢትዮጵያና ሩሲያ አዲስ አጋርነት እንዲሁም አቶ ነዋይ ገብረአብ ለተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ኮሚሽነርነት እንዲወዳደሩ በኢትዮጵያ መንግስት እጩ ሆነው ስለመቅረባቸውና በሌሎች ወቅታዊ የአገራችን ወቅታዊ ጉዳዮች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የጋዜጣዊ መግለጫው አንኳር ጉዳዮች ከቀጣዩን የቪዲዮ ሊንክ ይከታተሉ።
Source:: http://www.awrambatimes.com/?p=16432