ታሪክ እንደሚነግረን አፄ ሚኒሊክ ወታደሩ እረፍት ያድረግ ሰንቃንችንም እያለቀ ነው በሚል ልዩ ልዩ ምክንያቶች የኢትዮጵያ ጦር ተከዜን እንዳይሻገር አድረጉ መጨረሻው ምን እንደሆነ ሁላችንም እናውቀውለን። ከኤርትራ ጋር በተደረገው ጦርነትም የኢትዮጵያ ጦር ወደ አስመራ ገብቶ ከኤርትራ ሊመጣ የሚችለውን ሰጋት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ በድል እንዳይደመደም አቶ መለስ ዜናዊ ጦርነቱን በማስቆም አስራ ሰባት አመት ሙሉ ሀገራችን በጦርነት ሰጋት ውስጥ እንድትቆይ እና በኢኮኖሚያቸ እና በልማታችን ላይ ምን ያህል ተዕዕኖ እንዳሳደረ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። ታሪክ አሁንም እራሱን ደግሞ ከሁለቱም ጊዜ በከፋ ሁኔታ የሀገራችንን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል ፣ ህዝቧን ሰላም የሚያሳጣ ፣ ኢኮኖሚያዋን የሚያደቅ ፣ ልማትዋን የሚጎትት እና ከሁሉም በላይ የተግራይ አጎራባች ክልሎችን በሰጋት እና