![](https://ethiopia360.com/wp-content/uploads/2024/06/3671041-thumb-150x150.jpg)
![ECX Logo](https://www.2merkato.com//images/stories/ECX_Logo.jpg)
Here is the daily commodity trade data from Ethiopia Commodity Exchange (ECX) for items traded on 25 June 2024.
[…]
|
|||||||
ዋዜማ- የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ የመንግሥት እና የግል ድርጅት ሠራተኞች ውዝፍ ደሞዝ ላይ የስድስት ወራት ዕገዳ መጣሉን ዋዜማ ከምንጮቿ ተረድታለች። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ከጥቅምት 2013 ዓ.ም. እስከ ኅዳር 2015 ዓ.ም. ድረስ ላሉት ሃያ አምስት ወራት ሠራተኞቹ ያልተከፈላቸው ውዝፍ ደሞዝ፣ የመጨረሻ መፍትሄ እስከሚሰጠው ድረስ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለቀጣዩ ስድስት ወራት አልቀበልም ብሏል። ዋዜማ የተመለከተችው የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ ፊርማ ያረፈበት እና ለተለያዩ የክልሉ ቢሮዎች የተላከው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ በጉዳዩ ላይ መፍትሄ እስከሚሰጥ ድረስ ለባለፉት ስድስት ወራት ተጥሎ የነበረው ዕግድ ለተጨማሪ ስድስት ወራት ተራዝሟል። ደብዳቤው በጉዳዩ ላይ ወደ ፍርድ ቤት የሚቀርብ ጥያቄ እና በፍርድ ሂደት ላይ ያለ ጉዳይ፣ ጥናት ተደርጎ መፍትሄ እስከሚያገኝ ድረስ ተጥሎ የነበረው ዕግድ፣ የኢንዱስትሪ እና የፋይናንስ ቢሮዎች ባቀረቡት ጥያቄ ምክንያት ለተጨማሪ ስድስት ወራት ማራዘሙን ይገልጻል። በደብዳቤው ላይ እንደተመለከተው፣ ኢንዱስትሪ ቢሮው እስካሁን ስላደረገው ጥናት እንዲሁም ፋይናንስ ቢሮው በበጀት ጉዳይ ላይ እስከዛሬ ስለተደረጉ ጥረቶች ሪፖርት በማቅረብ የጥናት ጊዜው እንዲራዘምላቸው ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ጥያቄ አቅርበዋል። በዚህ መሰረትም፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ ባደረገው ስብሰባ፣ የጥናት ጊዜውን ለተጨማሪ ስድስት ወራት እንዲራዘመ መወሰኑ ታውቋል። ውዝፍ ደሞዝ ይከፈለን የሚለውን ጥያቄያቸውን ወደ ፍርድ ቤት እንዳይወስዱ ዕገዳ ከተጣለባቸው ድርጅት ሠራተኞች መካከል፣ አድዋ ከተማ የሚገኘው የአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ሠራተኞች ይገኙበታል። እነዚሁ የአልመዳ ፋብሪካ ሠራተኞች ለዋዜማ ባቀረቡት ቅሬታ ፣ ለስድስት ወራት ተጥሎ የነበረው ዕገዳ በተያዘው ወር ይነሳል በሚል ሲጠባበቁ ለተጨማሪ ስድስት ወር መራዘሙ አግባብ እንዳልሆነ አስረድተዋል። ‘ፋብሪካው ደሞዝ መክፈል ካቆመ ሦስት ዓመታት አልፎታል’ ያሉን የፋብሪካው ሠራተኞች፣ ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ከተከፈላቸው የጥቂት ወራት ደሞዝ በስተቀር እስካሁን ደሞዛቸው እንደተቋረጠ መሆኑን ለዋዜማ ነግረዋታል። ከዚህ ባለፈም፣ ከወራት በፊት ጥያቄያቸውን ወደ ፍርድ ቤት የወሰዱት የፋብሪካው ሠራተኞች፣ ፋብሪካው ካለው ንብረት ላይ የተወሰነውን በጨረታ ሸጦ ደሞዛቸውን እንዲከፈላቸው ፍርድ ቤቱ ቢወስንላቸውም፣ ጨረታውን ያሸነፈው ግለሰብ እስከአሁን ጨረታውን ያሸነፈበትን ብር ሊከፍል ባለመቻሉ ውሳኔው ተግባራዊ አለመደረጉን ይናገራሉ። “ደሞዛችንን ማግኘት ባለመቻላችን ለረሃብ፣ በሽታ፣ ስደት እና ልመና ተጋልጠናል” ሲሉም ምሬታቸውን ለዋዜማ ገልፀዋል። ፋብሪካው አሁን ላይ፣ ከጦርነቱ በፊት ከነበሩት አምስት ሺህ ገደማ ቋሚ ሠራተኞች መካከል፣ ወደ ሁለት ሺህ የሚደርሱትን ብቻ ወደ ሥራ እንዲመለሱ በማድረግ በከፊል ሥራ መጀመሩ ታውቋል። ከአልመዳ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ሠራተኞች በተጨማሪም፣ በኤፈርት ስር በሚተዳደሩት ሌሎች ድርጅቶች ዘንድም በተመሳሳይ ችግር ውስጥ የሚገኙ ሠራተኞች መኖራቸውን ዋዜማ ተገንዝባለች። ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ በክልሉ የሚኖሩ አንድ ጠበቃ በበኩላቸው፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ሠራተኞቹ በጦርነቱ ወቅት ያላገኙትን የውዝፍ ደሞዝ ጥያቄ ላለመመለስ ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚቃረን ደንብ ማውጣቱን ለዋዜማ ገልጸዋል። እኒሁ ጠበቃ፣ ለዚሁ ተብሎ በጊዜያዊ አስተዳደሩ በቅርቡ ወጥቷል ባሉት ‘ደንብ 4/2016’ መሰረት፣ ሠራተኞቹ በጦርነቱ ወቅት ያልተከፈላቸውን ውዝፍ ደሞዝ በተመለከተ ክስ ከማቅረብም ሆነ ከመጠየቅ ይታገዳሉ። እንደ ዋዜማ ምንጮች ገለጻ፣ ከመንግሥት ሠራተኞች ይልቅ በኤፈርት ስር ያሉ የተለያዩ ድርጅት ሠራተኞች፣ በጦርነት ወቅት ያልተከፈላቸውን ውዝፍ ደመወዝ ለማግኘት ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት በመውሰድ ክስ መስርተው ነበር። በክልሉ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች በተለይ ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ደሞዛቸው በቋሚነት እየተከፈላቸው ሲሆን፣ የድርጅቶች እና ፋብሪካዎች ሠራተኞች ግን አብዛኞቹ ደሞዛቸው እስከአሁን ተቋርጦ እንደሚገኝ ተሰምቷል። ከክልሉ መንግሥት በኩል የኢንዱስትሪ ሠራተኞች ደሞዝ እስከአሁን የተቋረጠበት ምክንያት፣ ተቋማቱ በጦርነቱ ወቅት በደረሰባቸው ጉዳት የተነሳ በቀላሉ ማገገም እና ወደ ሥራ መመለስ ባለመቻላቸው ነው ። ዋዜማ በጉዳዩ ላይ የክልሉን ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊዎች ለማናገር ጥረት ያደረገች ሲሆን፣ አንድ የቢሮው ኃላፊም፣ ስለጉዳዩ ሲወራ ከመስማታቸው በስተቀር መቼ እና እንዴት እንደተወሰነ እንደማያውቁ ነግረውናል። የመንግሥት ሠራተኞች እና የግል ድርጅት ተቀጣሪዎች በጦርነቱ ወቅት ስላልተከፈላቸው ደመወዝ የሚያነሱት ጥያቄ ላይ ለስድስት ወራት ዕግድ የተጣለ መሆኑን ግን፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ካሰራጨው ደብዳቤ ‘እንደተገነዘቡ’ ገልጸዋል። ኃላፊው አክለውም፣ ዋዜማ የተመለከተችው የጌታቸው ረዳ አስተዳደር ደብዳቤ ላይ እንደተጠቀሰው፣ ኢንዱስትሪ ቢሮው ተጥሎ የነበረው ዕገዳ ለተጨማሪ ስድስት ወራት ይራዘምልኝ ብሎ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ጥያቄ ማቅረቡን ጭምርም እንደማያውቁ ተናግረዋል። ሆኖም ጉዳዩን ሊያውቁ የሚችሉት የቢሮው አመራሮች ስለሚሆኑ እነሱ ሃሳብ ቢሰጡ የተሻለ እንደሚሆን የገለጹልን ቢሆንም፣ የኢንዱስትሪ ቢሮው ኃላፊ፣ በተደጋጋሚ የተደወለላቸውን ስልክ ባለማንሳታቸው ሃሳባቸውን ማካተት አልተቻለም። ጊዜያዊ አስተዳደሩ በተቋቋመበት ወቅት፣ በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ለሁለት ዓመት ደሞዝ ያልተከፈላቸው የመንግሥት እና የግል ሠራተኞች ደሞዛቸውን እንዲያገኙ ጥረት እንደሚያደርግ መግለፁ ይታወሳል። [ዋዜማ] The post የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውዝፍ የደሞዝ ጥያቄ ላይ የስድስት ወራት ገደብ ጣለ first appeared on Wazemaradio. The post የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውዝፍ የደሞዝ ጥያቄ ላይ የስድስት ወራት ገደብ ጣለ appeared first on Wazemaradio. […] ![]() ![]() ዋዜማ- ባለፉት ዓመታት በመቶ ቢሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ከብሄራዊ ባንክ የወሰደው መንግስት ከዚህ በኋላ እንደፈለገ የሚበደርበትን አሰራር የሚከለክል አዲስ ረቂቅ አዋጅ ለተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ። ዋዜማ የተመለከተችው ረቂቅ አዋጅ እንዳሰፈረው መንግስት የከፋ ችግር ካልገጠመው በቀር ከብሄራዊ ባንክ ያለገደብ የሚበደርበት አሰራር ከዚህ በኋላ በህግ የተከለከለ ይሆናል። ይህ ድንጋጌ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ተካቶ የቀረበ ሲሆን በረቂቅ አዋጁ ክፍል አምስት በብሔራዊ ባንክ እና በመንግስት መካከል የሚኖረውን ግንኙነት ባተተበት ምእራፍ ውስጥ ተካቷል። “በአዋጁ በግልጽ ካልተፈቀደ በስተቀር ብሔራዊ ባንክ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለፌዴራል ; ለክልል ; ለማንኛውም የታችኛው የመንግስት የአስተዳደር እርከን ፣ የከተማ አስተዳደር ወይም የመንግስት ተቋም ብድር መስጠት አይችልም ” ይላል። የፌዴራል መንግስት ከብሔራዊ ባንክ ሲወስድ የቆየው ቀጥተኛ ብድር (Direct advance)በሚባል የሚታወቀው የብድር አይነት የገንዘብ ህትመትን በማበረታታት ለሀገሪቱ የዋጋ ንረት መባባስ ከዋነኞቹ ምክንያቶች ውስጥ ይጠቀሳል። በአዋጁ ማብራሪያ ላይ እንደተጠቆመው በመንግስት ከብሄራዊ ባንክ ጋር ያለው የብድር ግንኙነት በግልጽ ተደንግጎ አለመቀመጡ ችግር መፍጠሩን ያነሳል። ከ1995 ዓ.ም አንስቶ እስከ 2000 ዓ.ም ድረስ መንግስት ከብሔራዊ ባንክ በሚወስደው የብድር መጠን እና የአከፋፈል ሁኔታ እንዲሁም ወለዱ በሚሰላበት አግባብ ላይ ግልጽ ድንጋጌ እንደነበር የጠቀሰው የአዋጁ ማብራሪያ ፣ ነገር ግን እነዚህ መንግስት ከብሔራዊ ባንክ ብድር የሚወስድበትና የሚከፍልበትን እንዲሁም ወለድ የሚሰላበት ድንጋጌ ከ2000 ዓ.ም ወዲህ እንዲወጡ መደረጉንም አንስቷል። ብዙዎች እነዚህ ገደቦች መነሳታቸው መንግስት በተለይም የፌዴራል መንግስት ከብሄራዊ ባንክ ያለ መጠን እና ያለ መክፈያ ጊዜ ገደብ እንዲበደር እንዳደረገው እና ከብሔራዊ ባንክ የሚወሰድ ብድር ደግሞ ሌሎች ባንኮች እንደሚያደርጉት ከገበያ የተሰበሰበ ሳይሆን በኢኮኖሚ ውስጥ ያልነበረ እና ከምርት ጋር የማይገናኝ በመሆኑ የዋጋ ንረት እንዲባባስ መንገድን ከፍቷል ። የፌዴራል መንግስት ከብሔራዊ ባንክ በዚህ መንገድ በመቶ ቢሊየን ብሮች ተበድሮ ወደ ገበያ ማስገባቱ እና እነዚህ ብድሮችም አለመመለሳቸውን ለጉዳይ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባለፈው አመት ሀምሌ ወር ላይ ባወጣው መመሪያ የፌዴራል መንግስት በ2016 ዓ.ም ከብሔራዊ ባንክ መበደር የሚችለው በ2015 ዓ.ም የተበደረውን አንድ ሶስተኛውን ብቻ እንዲሆን ገድቦት ቆይቷል።አሁን በማእከላዊ ባንኩ ረቂቅ አዋጅ ላይ ብድርን ለመንግስት መስጠት እንደማይችል አስቀምጧል። ሆኖም ለፓርላማው የቀረበው ረቂቅ አዋጅ መንግስት ከብሔራዊ ባንክ የሚበደርበትን መንገድ ሙሉ ለሙሉ አልዘጋውም። በዚህም ብሔራዊ ባንክ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ላይ የተመሰረተ ጊዜያዊ የኦቨር ድራፍት አገልግሎት (የመንግስት ሂሳብ እየታየ በአንድ አመት ውስጥ የሚከፍለው የአጭር ጊዜ ጊዜ ብድር ) እንደሚሰጠው ይጠቅሳል። ይህም ግን ሁለት ገደቦች ተጥለውበታል። አንዱ በዚህ መልኩ የሚሰጠው ብድር የፌዴራል መንግስት ያለፉት ሶስት አመታት ገቢው አማካዩ ተወስዶ ፣ የአማካዩ 15 በመቶ መሆኑ እና ፣ መንግስት በቀጣይ አመት ተመሳሳይ የኦቨር ድራፍት ብድር መውሰድ ከፈለገ ቀድሞ የወሰደውን ብድር የግድ መመለስ እንዳለበትም ግዴታ ተቀምጧል። በገንዘብ ፖሊሲ ተመን ላይ ተመስርቶ የሚመሰለ ወለድም ይታሰብበታል። መንግስት ከተቀመጠለት በላይ ብድር መጠየቅ የሚችለውም ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ሲያጋጥም ; ማለትም ያልጠበቀ የማህበረሰብ ጤና ችግር ፣ የተፈጥሮ አደጋ ፣ ድርቅ ወይንም አጠቃላይ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወይንም በፌዴራል መንግስት ገቢ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ የውጭ ኢኮኖሚ ለውጦች ሲኖሩ መሆኑም ተጠቅሷል። ረቂቅ አዋጁም ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ በትላንትናው እለት ተመርቷል። [ዋዜማ] The post ብሄራዊ ባንክ ለመንግስት ቀጥታ ብድር እንዳይሰጥ የሚከለክል ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ first appeared on Wazemaradio. The post ብሄራዊ ባንክ ለመንግስት ቀጥታ ብድር እንዳይሰጥ የሚከለክል ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ appeared first on Wazemaradio. […] ![]() ![]() ዋዜማ-በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የፋኖ ታጣቂዎች በተቆጣጠሯቸውና ወጣ ገባ በሚሉባቸው ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት እንዲቋረጥ መደረጉን ዋዜማ ተረድታለች፡፡ በዞኑ የባንክ አገልግሎት ከተቋረጠባቸው ወረዳዎች መካከል መንዝ ላሎ፣ ግሼ ራቤል፣ አንፆኪያ ገምዛና ቀወት እንደሚገኙበት ዋዜማ በየወረዳዎቹ የባንክ ቅርንጫፎች አረጋግጣለች፡፡ የባንክ አገልግሎቱን በተጠቀሱት ወረዳዎች እንዲያቋርጡ የተገደዱት የግል ባንኮች ጭምር መሆናቸውን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በተጠቀሱት ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት የተቋረጠው ካለፈው አርብ ሰኔ 7/2016 ዓ.ም ጀምሮ መሆኑን ዋዜማ ተረድታለች፡፡ ከአርብ ጀምሮ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ስዓት ድረስ በመንዝ ላሎ ወረዳ ወገሬ ከተማ፣ በግሼ ራቤል ወረዳ ራቤል ከተማ፣ በአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ መኮይ ከተማና ቀወት ወረዳ ራሳ ከተማ ባንኮች እንደተዘጉ ናቸው፡፡ በአንጻሩ የአንጾኪያ ገምዛ ወረዳ አካል በሆነችው ማጀቴ ከተማ ባንኮች አገለግሎት መስጠት መቀጠላቸውን ዋዜማ ከከተማዋ ነዋሪዎች ሰምታለች፡፡ ምንም እንኳን በከተማዋ አገልግሎት ባይቋረጥም ባንኮች ለደንበኞቻቸው የሚሰጡት ወጪ ገደብ ተጥሎበታል ተብሏል፡፡ አገልግሎቱ የተቋረጠው ባንኮቹ ድንገተኛ ትዕዛዝ ከመንግሥት አካል ከደረሳቸው በኋላ መሆኑን፣ የየወረዳዎቹ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የግል ባንኮች ሰራተኞች ለዋዜማ ተናግረዋል፡፡ ድንገተኛ የተባለው ትዕዛዝ ለባንኮቹ የተላለፈው የሸዋ ቀጠናን ከሚመራው ኮማንድ ፖስት መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በተጠቀሱት ከተሞች የሚገኙ የባንኮች ቅርንጫፎች የኮማንድፖስቱ ትዕዛዝ የደረሳቸው በየዲስትሪክቶቻቸው በኩል መሆኑ ጠቁመዋል፡፡ ባንኮቹ ከኮማንድ ፖስቱ የደረሳቸው ትዕዛዝ “ኮማንድ ፖስቱ አካባቢውን ከጽንፈኞች እስከሚያጸዳ ድረስ አገልግሎት አቁሙ” በሚል የተገለጸ መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ምንም አንኳን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈጻሚነት ጊዜ ቢያበቃም አካባቢው በወታደራዊ ኮማንድ ፖስት መመራቱን ቀጥሏል፡፡ ባንኮች ሥራ እንዲያቆሙ በኮማንድ ፖስቱ አማካኝነት ትዕዛዝ የተላለፈውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈጻሚነት ቀን ገደብ ከባቃ በኋላ ነው፡፡ ዋዜማ ስለ ጉዳዩ የባንክ አገልግሎት የተቋረጠባቸው ወረዳዎች የሚገኙበት ሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የቀጠናው ኮማንድ ፖስት አባል አቶ መካሽ አለማየሁን ለማነጋገር ሞክራለች፡፡ ይሁን እንጅ የዞኑ አስተዳዳሪ ስልክ አንተው ካነጋገሩን በኋላ ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጡ ስልክ ዘግተዋል፡፡ ስልኩ ከተቋረጠ በኋላ በድጋሚ ቢደወልላቸውም ባለመመለሳቸው ከመንግሥት ወገን ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ አገልግሎት የተቋረጠባቸው ቅርንጫፎች ላይ ይሰሩ የነበሩ የባንክ ሰራተኞች ወደሌላ ሌላ ቦታ ሥራ እየተመደቡ ነው ተብሏል፡፡ ለአብነትም የመንዝ ላሎ ወረዳ ወገሬ ከተማ ቅርንጫፍ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰራተኞች፣ ወደ መንዝ ማማ ወረዳ ምላሌ ከተማ ቅርንጫፎች ተዘዋውረው ሥራ መጀመራቸውን ለዋዜማ አረጋግጠዋል፡፡ በተጠቀሱት ከተሞች የሚገኙ ባንኮች በዕለቱ ትዕዛዙ ከደረሳቸው በኋላ የቀኑን ሂሳባቸውን ዘግተው፣ ወዲያ አገልግሎት ማቆማቸውን የየቅርጫፎቹ ሰራተኞች ተናግረዋል፡፡ የባንክ አገልግሎት ከተቋረጠባቸው ወረዳዎች መካከል የመንዝ ላሎ ወረዳ ወገሬ ከተማን ጨምሮ፣ የግሼ ወረዳው ከተማ ራቤልን ጨምሮ፣ ይህ ዘገባ እስከ ተጠናቀረበት ስዓት ድረስ በፋኖ ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር መሆናቸውን ዋዜማ ከአየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች ሰምታለች፡፡ ሌላኛው የባንክ አግልግሎት የተቋረጠበት የአንጾኪያ ገምዛ ወረዳ መቀመጫ መኮይ ከተማ በመንግሥት ኃይሎች ቁጥጥር ስር መሆኗን ዋዜማ ተረድታለች፡፡ የመንግሥት ኃይሎች ከተማዋን የተቆጣጠሩት በዚሁ ሳምንት ሲሆን፣ ከዚያ በፊት የፋኖ ታጣቂዎች ከተማዋን ተቆጣጥረው መሰንበታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ [ዋዜማ] The post በፀጥታ ምክንያት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባንክ አገልግሎት ተቋረጠ first appeared on Wazemaradio. The post በፀጥታ ምክንያት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባንክ አገልግሎት ተቋረጠ appeared first on Wazemaradio. […] |
News
Political Groups |