Here is the daily commodity trade data from Ethiopia Commodity Exchange (ECX) for items traded on 22 April 2024.
[…]
|
|||||||
Photo —FILE ዋዜማ – ሕወሓት ከአራት ዓመት በፊት “ሕገ – ወጥ ነው” ያለውን ገዥውን ፓርቲ ብልፅግና ለመቀላቀል ተከታታይ ድርድሮች እያደረገ መሆኑን ዋዜማ ከተለያዩ ምንጮች ያሰባሰበችው መረጃ ያመለክታል። ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የፈረመው ሕወሓት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በሊቀመንበርነት የሚመሩትን ብልፅግናን በመቀላቀል በሀገራዊ ጉዳዮች አብሮ ለመስራት መስማማቱን ቢገልፅም ፓርቲውን ለመቀላቀል ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል። ከብልፅግና በፊት የነበረው ኢሕአዴግ እኩል የስራ አስፈፃሚና ማዕከላዊ ኮሚቴ ውክልና ያላቸው አራት ንዑስ ፓርቲዎች ጥምረት ሲሆን ብልፅግና ግን አንድ ወጥ ፓርቲ ነው። የብልፅግና የፓርቲ ውክልና በህዝብ ብዛት የሚወሰን እንጂ እንደ ኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች እኩል ውክልና አይኖራቸውም። አሁን እየተደረገ ባለው ድርድር ሕወሓት የብልፅግና ፓርቲ ሕገ-ደንብ ተሻሽሎ በፓርቲ ውስጥ አባል ድርጅቶች እኩል የማዕከላዊ ኮሚቴና የስራ አስፈፃሚ ውክልና እንዲኖራቸው ይፈልጋል። ብልፅግና ግን ሕወሓት የተናጠል ህልውናውን አክስሞ ብልፅግናን እንዲቀላቀልና ውክልናውም በትግራይ ህዝብ ቁጥር ልክ የሚወሰን መሆኑን ይገልፃል። የሕወሓት ሊቀ መንበር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል በአዲስ አበባ ተገኝተው ይህን ድርድር የጀመሩት ሲሆን ከሁለት ሳምንት በኋላ የብልፅግና ምክትል ሊቀመንበር አደም ፋራህ ወደ መቀሌ ተጉዘው በጉዳዩ ላይ በስፋት ተነጋግረዋል። በሕወኋት በኩል ብልፅግናን መቀላቀል “ስህተት ነው …አስፈላጊም አይደለም” ብለው የሚያምኑ አመራሮች ቢኖሩም፣ ውህደቱ ለትግራይ ችግሮች መፍትሄ ለማምጣት ጠቀሜታ አለው፣ በተለይም የትግራይን ፀጥታና ደህንነት ለመስጠበቅ ከብልፅግና ጋር አብሮ መቆም አስፈላጊ ነው ብለው የሚያምኑም አሉ። በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ዝርዝር ለማንበብ ይህን ማስፈጠሪያ ተጭነው ለቤተኛ አንባቢዎቻችን ያዘጋጀነውን ማመላከቻ ያንብቡ The post ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው first appeared on Wazemaradio. The post ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው appeared first on Wazemaradio. […] With a vast customer base exceeding 4.6 million nationwide, comprising over 3.75 million post-paid users alongside 900,000 prepaid customers, EEU revealed that it was working towards enhancing its technological infrastructure. The company is poised to address long-standing challenges for its prepaid customers and enhancing convenience through the development of a cutting-edge technology center valued at USD 48 million. […] ዋዜማ- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ ከአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም ፊት ለፊት ለኮሪደር ልማት በሚል የፈረሱ ሰፈሮችን ጨምሮ ከ250 በላይ በሚሆኑ ቦታዎች ላይ የሊዝ ጨረታ ማውጣቱን ዋዜማ ከተመለከተችው የጨረታው ሰነድ ተረድታለች። የሊዝ ጨረታው ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ውጭ በተቀሩት የከተማው አስር ክፍለ ከተሞች ባሉ ቦታዎች ላይ ወጥቷል። የሊዝ ጨረታው ለአመታት ከተቋረጠ በኋላ ሲወጣ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። የጨረታው ሰነድም ከረቡዕ ሚያዝያ 9 2016 አ.ም ጀምሮ መሸጥ የተጀመረ ሲሆን ፣ የሰነድ ሽያጩ እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2016 አ.ም ድረስ እንደሚቀጥል ተነግሯል። ለሊዝ የቀረበ ከፍተኛ ቦታ ያቀረበው ክፍለ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ሲሆን ቦሌ እና ቂርቆስ ክፍለ ከተሞች አንድ አንድ ቦታ ለሊዝ ጨረታ ቀርቦባቸዋል። በኮሪደር ልማት በፈረሰው የአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም አካባቢ 22 ቦታዎች ለሊዝ ጨረታ ቀርበዋል። በዚህ አካባቢ ትልቁ ለሊዝ የቀረበው ቦታ 2,179 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን ፣ ዝቅተኛ ስፋት ያለው መሬት ደግሞ 650 ካሬ ሜትር ነው። በደረጃ አንድ ለተመደቡት ለ22ቱም ቦታዎች የሊዝ መነሻ ዋጋ በካሬ 2,213.25 ብር ተቆርጦላቸዋል። ለአንድ ካሬ ከፍተኛ መነሻ ዋጋ የተቆረጠላቸውም እነዚሁ በአራዳ ክፍለ ከተማ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም አቅራቢያ ላሉት ቦታዎች ነው።ንፋስ ስልክ ላፍቶ ከፍለ ከተማ በመጠን ብዙ (ከ150 በላይ ቦታዎችን) በማቅረብ ቀዳሚው ነው። የጨረታ ሰነዱ 2,300 ብር እየተሸጠ ሲሆን ፣ ጨረታው ከሚያዝያ 28 2016 አ.ም ጀምሮ ለዘጠኝ ተከታታይ ቀናት ይከፈታል ተብሏል። የጨረታ አሸናፊዎች ቅድመ ክፍያ ያሸነፉበትን መሬት 40 በመቶ ሲሆን ቀሪው 60 በመቶ ክፍያ በአምስት አመታት ውስጥ ተከፍሎ እንዲጠናቀቅ ይጠበቃል። የሊዝ ዘመኑም ለ60 አመታት ነው። ሁሉም ለጨረታ የቀረቡ ቦታዎቹም ለቅይጥ አገልግሎት እንዲውሉ ታስቦ ነው። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሁኑን የሊዝ ጨረታ ያወጣው ባለፈው አመት መጨረሻ አካባቢ ከወጣው የሊዝ ጨረታ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። በ2015 አ.ም ግንቦት ወር ላይ የከተማ አስተዳደሩ 297 ቦታዎችን ለጨረታ አቅርቦ ነበር። በኋላ ላይ የአስሩ ቦታዎች ጨረታ ተሰርዞ የ287ቱ ቦታዎች የጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር ነበር የወጣው።ሆኖም በ2015 አ.ም ሰኔ ወር አጋማሽ አካባቢ ጨረታው ሲከፈት በተለያዩ ቦታዎች ለአንድ ካሬ ቦታ የተሰጠው ዋጋ በእጅጉ ተጋኖ የታየበት ሁኔታ ነበር። በካሬ ከ690 ሺህ ብር በላይ ዋጋ የቀረበበት ቦታም ነበር። እንዲሁም የ287 ቦታዎች የሊዝ ጨረታን አንደኛ ዋጋ አቅርበው ካሸነፉት ውስጥ ውል ፈጽመው ቦታውን የተረከቡት ከግማሽ በታች የሆኑት 131 አሸናፊዎች ብቻ ነበሩ። 156ቱ አሸናፊዎች ውሉን ፈርመው መሬቱን አልተረከቡም። ይህም በወቅቱ መነጋገርያ ነበር። በዚህ ሳቢያ የከተማ አስተዳደሩ መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ 156ቱን ቦታዎች ሁለተኛ ላይ የተቀመጡ አሸናፊዎች አንደኛ የሆኑት ተጫራቾች ባስቀመጡት ዋጋ መሬቱን እንዲረከቡም ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል። የከተማ አስተዳደሩ ከመሬት ሊዝ ሽያጩ ሊያገኝ አቅዶ የነበረውን 12 ቢሊየን ብር ነበር። [ዋዜማ] The post በፒያሳ ለኮሪደር ልማት የፈረሱ ሰፈሮችን ጨምሮ በከተማው በርካታ ቦታዎች የሊዝ ጨረታ ወጣ first appeared on Wazemaradio. The post በፒያሳ ለኮሪደር ልማት የፈረሱ ሰፈሮችን ጨምሮ በከተማው በርካታ ቦታዎች የሊዝ ጨረታ ወጣ appeared first on Wazemaradio. […] In a bold move designed to boost economic growth, Ethiopia took a major shift in its trade policy. The Ethiopian Investment Commission (EIC) and the Ministry of Trade and Regional Integration jointly revealed that export, import, wholesale, and retail trade sectors would now be open to foreign companies. […] |
News
Political Groups |